Wednesday, June 7, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ታኅሣሥ ሦስት ይጀምራል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ታኅሣሥ ሦስት ይጀምራል

ቀን:

የዘንድሮ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ታኅሣሥ 3 ቀን 2013 ዓ.ም. በተመረጡ ስታዲየሞች እንደሚጀመር የሊጉ አክሲዮን ማኅበር አስታወቀ፡፡ ውድድሩን በቀጥታ ስርጭት ለማስተላለፍ ያሸነፈው ዲኤስቲቪ የባለሙያዎች ቡድን ቅድመ ዝግጅት ለማድረግ ባለፈው ባለፈው ሐሙስ ምሽት አዲስ አበባ መግባቱ ታውቋል፡፡

ቀደም ሲል የፕሪሚየር ሊጉን ስያሜ ጨምሮ በአጠቃላይ ወደ 68 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ማግኘት የቻለበትን ስምምነት ከዲኤስቲቪ ጋር መፈራረሙን ያስታወቀው የፕሪሚየር ሊጉ አክሲዮን ማኅበር፣ በአሁኑ ወቅትም ውድድሮቹ የሚደገረጉባቸውን የተመረጡ ስታዲየሞች የዲኤስቲቪ ሙያተኞችን በማካተት ጭምር በመገምገም ላይ ይገኛል፡፡

ጨዋታው የሚደረግባቸው ስታዲየሞች በአጠቃላይ ስድስት ሲሆኑ፣ የአዲስ አበባ ስታዲየምን ጨምሮ የመቐለ፣ የባህር ዳር፣ የጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ የሐዋሳና የድሬዳዋ ስታዲየሞች መሆናቸውም ታውቋል፡፡ ቡድኑ እሑድ ጥቅምት 22 ቀን 2013 ዓ.ም. የባህር ዳር ስታዲየምን እንደሚጎበኝ አክሲዮን ማኅበሩ አስታውቋል፡፡ 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ኢዜማ ከለቀቁ አባላት ግማሽ ያህሉ የዲሲፒሊን ችግር የነበረባቸው ናቸው አለ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በቅርቡ ከፓርቲው አባልነት ለቀናል...

የአዲስ አበበ መምህራን ማኅበር የደመወዝ ጥያቄው ምላሽ ካላገኘ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደሚያቀርብ አስታወቀ

የአዲስ አበባ መምህራን ማኅበር ለረጅም ዓመት ያገለገሉ መምህራን ደመወዝና...

ኢሰመኮ በዩኒቨርሲቲዎች የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ጉዳይ የሚመራበት የጽሑፍ ፖሊሲ አለመኖሩን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች...