Wednesday, June 7, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትዋሊያዎቹ ነገ ዛምቢያን ይገጥማሉ

ዋሊያዎቹ ነገ ዛምቢያን ይገጥማሉ

ቀን:

ለወራት ከአኅጉራዊና ከዓለም አቀፍ ውድድሮች ርቆ የነበረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) ነገ ሐሙስ ጥቅምት 12 እና እሑድ ጥቅምት 15 ቀን 2013 ዓ.ም. ከዛምቢያ አቻው ጋር ሁለት የወዳጅነት ጨዋታዎችን ያደርጋል፡፡ በብሔራዊ ፌዴሬሽኙ በተሾመው አዲሱ የዋሊያዎቹ አሠልጣኝ ውበቱ አባተ ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾቹ፣ በካፍ አካዴሚ ዝግጅታቸውን ከጀመሩ ሳምንታት ያስቆጠሩ ሲሆን፣ የነገው የወዳጅነት ጨዋታው ቡድኑ ያለበትን አቅም ለማወቅና ጠንካራ ቡድን ለማግኘት ይረዳዋል ተብሏል፡፡ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከአይቮሪኮስት፣ ማዳጋስካርና ኒጀር ጋር የተመደበው ብሔራዊ ቡድኑ ባደረጋቸው ሁለት ጨዋታዎች በማዳጋስካር ተረትቶ፣ አይቮሪኮስትን 2 ለ 1 በመርታት በሦስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል፡፡ ከዛምቢያ ጋር የሚያደርገው ግጥሚያ በቅርቡ ከኒጀር ጋር ለሚኖረው የማጣሪያ ጨዋታ አቅሙን ያጠናክርበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የዛምቢያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ረቡዕ ጥቅምት 11 ቀን ቦሌ ኢንተርናሽናል ኤርፖርት እንደሚደርስ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዲስ አበበ መምህራን ማኅበር የደመወዝ ጥያቄው ምላሽ ካላገኘ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደሚያቀርብ አስታወቀ

የአዲስ አበባ መምህራን ማኅበር ለረጅም ዓመት ያገለገሉ መምህራን ደመወዝና...

ኢሰመኮ በዩኒቨርሲቲዎች የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ጉዳይ የሚመራበት የጽሑፍ ፖሊሲ አለመኖሩን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች...

ንግድ ባንኮች በከፍተኛ የገንዘብ እጥረት ውስጥ መሆናቸው ተገለጸ

‹‹የገንዘብ እጥረት የሚገጥመው ያለውን ሀብት የማስተዳደር ችግር ስላለ ነው›› የኢትዮጵያ...