Sunday, June 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊበአዲስ አበባ ከባድ ተሽከርከሪዎችን በተከለከለ ሰዓት የሚያንቀሳቅሱ ከብር 5 መቶ እስከ 6...

በአዲስ አበባ ከባድ ተሽከርከሪዎችን በተከለከለ ሰዓት የሚያንቀሳቅሱ ከብር 5 መቶ እስከ 6 ሺህ እንዲቀጡ መወሰኑ ተገለፀ

ቀን:

ከባድ ተሽከርካሪዎችን በተከለከለ ሰዓት ወደ አዲስ አበባ ከተማ ማስገባት እና ማንቀሳቀስ ከብር 500 እስከ 6 ሺህ ብር እንደሚያስቀጣ የከተማዋ ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው ለሪፖርተር በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ከባድ ተሽከርከሪዎችን ከቀኑ 1000 እስከ 200 ሰዓት ወደ ከተማዋ ማስገባትና ማንቀሳቀስ እንደማይቻል ገለጿል።

ይህንን በሚተላለፉ አሽከርካሪዎች ላይ ከብር 5 መቶ እስከ 6 ሺህ እንደሚቀጡ የትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል

ቢሮው በሥራ መውጫ ሰዓታት ላይ የሚታየውን ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅና አደጋ ለመቀነስ የከባድ ተሽከርካሪዎችን እንቅስቃሴ መወሰን የሚያስችል መመሪያ ተግባራዊ ማድረጉን አመልክቷል።

በዚሁም መሰረት የመጫን አቅማቸው ከ2.5 ቶንና ከዚያ በላይ የሆኑ ተሽከርካሪዎች እንደጥፋቱ ክብደትና ድግግሞሽ ከብር 5 መቶ እስከ 6 ሺህ እንዲሁም በተደራቢነት 1 እስከ 3 ወር የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ እንደሚያግድ መመሪያው ያትታል።

የመንቀሳቀሻ ፈቃድ ሳያወጡ በተከለከለው ሰዓት ወደከተማዋ ማስገባትና በከተማዋ ውስጥ ማንቀሳቀስ እንዲሁም በዋና መንገድ ላይ ጭነት መጫንና ማውረድ ተግባር የፈፀመ ለመጀመሪያ ጊዜ ብር 1 ሺህ፣ ለሁለተኛ ጊዜ ደግሞ ብር 2 ሺህ እንዲሁም ከሁለት ጊዜ በላይ ድርጊቱን ከፈፀመ ብር 3 ሺህ ተቀጥቶ የአሽከርካሪው መንጃ ፈቃድ ለአንድ ወር እንደሚታገድ ይገልጻል፡፡

በሌላ በኩል ጊዜ ያለፈበት የመንቀሳቀሻ ፈቃድ ይዞ ወደከተማዋ ማስገባት ወይም በከተማዋ ውስጥ ማንቀሳቀስ ለመጀመሪያ ጊዜ ብር 5 መቶ እና ለሁለተኛ ጊዜ ደግሞ ብር 1 ሺህ፤ ድርጊቱ ለሶስተኛ ጊዜ ከተፈፀመ ብር 4 ሺህ ተቀጥቶ የአሽከርካሪው መንጃ ፈቃድ 2 ወር ይታገዳል ይላል፡፡

በተጨማሪም የተሰረዘ ወይም የተደለዘ ወይም አስመስሎ የተሰራ የመንቀሳቀሻ ፈቃድ ይዞ መገኘትና መጠቀም እንዲሁም የመንቀሳቀሻ ፈቃዱን ለሌላ አካል አሳልፎ መስጠት ብር 6 ሺህ እንደሚያስቀጣ ያስረዳል፡፡

በመሆኑም የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የተከለከለውን ሰዓት ታሳቢ በማድረግ የትራፊክ መጨናነቅንና አደጋን ለመቀነስ ትብብር እንድታደርጉ ቢሮው የላከው መግለጫ አሳስቧል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...