Friday, June 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየአዲስ አበባ ኮቪድ-19 ፊልድ ሆስፒታል ሥራ ጀመረ

የአዲስ አበባ ኮቪድ-19 ፊልድ ሆስፒታል ሥራ ጀመረ

ቀን:

የኮሮና ቫይረስ መመርመርያ ኪት ማምረቻም ተመርቋል

በዓለም የምግብ ፕሮግራም ድጋፍና በጤና ሚኒስቴር አስተባባሪነት የተገነባው የአዲስ አበባ የኮቪድ-19 ፊልድ ሆስፒታል ሥራ ጀመረ፡፡

ሁለት መቶ የኮቪድ-19 ፅኑ ሕሙማንን ለማስተናገድ የሚችለው ሆስፒታል በቦሌ ቡልቡላ አካባቢ የሚገኝ ሲሆን በይፋ ሥራ ያስጀመሩትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (/) ናቸው፡፡

ሆስፒታሉ በተለይም በኮሮና በሽታ ተይዘው የጸና የሕመም ምልክት ለሚያሳዩ  ሕሙማን የሕክምና አገልግሎትሚሰጥ ሲሆን የሕክምና መሣሪያዎችም  ተሟልቶለታል፡፡

በተያያዘ ዜና በኢትዮጵያ የመጀመርያ የሆነው የኮረና ቫይረስ የላቦራቶሪ  መመርመርያ ኪት ማምረቻ ፋብሪካ ተመርቋል::

በኢትዮጵያበቻይና ቢጂአይ ሄልዝ ትብብር የተቋቋመውን ፋብሪካ የመረቁት ጠቅላይ ሚኒስትርብይየፋብሪካው መገንባት በአፍሪካስተኛ ደረጃ ላይ የደረሰውን  የኢትዮጵያ የመመርመር አቅም በማሳደግ የተሻለ የመከላከል ሥራ ለመሥራት እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡ 

ፋብሪካው ለነዋሪዎችና በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ለሚያልፉ መንገደኞች በክፍያ የላብራቶሪ አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ለውጪ አገሮች በሚደረገው ሽያጭም  የአፍሪካ አገሮች ቅድሚያ የሚያገኙ ይሆናል።

በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪያል ፓርክ የተገነባው ፋብሪካ በዓመት አሥር ሚሊዮን ኪቶችን እንደሚያመርትና የኮቪድ-19 ሥርጭት ከተገታ በኋላ፣ የሳንባ ነቀርሳ እንዲሁም ሌሎች የሪል ታይም (አርቲ) ፒሲአር መመርመርያ ኪቶችን ጨምሮ ሌሎች ኒዮክሊክ አሲድን (ዲኤንኤ እና አርኤንኤ) መለያ ኬሚካሎችን ወደ ማምረት የሚሸጋገር ይሆናል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...