Thursday, June 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊበኮሮና ቫይረስ

በኮሮና ቫይረስ

ቀን:

ከ0 – 4 ዓመት ያሉ ከ640 በላይ ሕፃናት

ከ5 – 14 ዓመት ያሉ ከ780 በላይ ልጆች ተይዘዋል

ለዓለም ፈታኝ የሆነው የኮሮና ቫይረስ ወደ ኢትዮጵያ ከገባ ከመንፈቅ ወዲህ በቫይረሱ የሚያዙናይወታቸውን የሚያጡ ኢትዮጵያውያን ቁጥር እየጨመረ ይገኛል፡፡ እስከ መስከረም 4 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ 64,786 ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 1022 ሆኗል፡፡

ከእነዚህም ወስጥ እስከ መስከረም 3 ቀን ድረስ ባለው መረጃ 644 የሚሆኑት 0 እስከ 4 ዓመት ያሉ ሕፃናት ሲሆኑ፣ 788 ያህሉ ደግሞ አምስት እስከ 14 ዓመት ያሉ ልጆች ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ላይ እንዳስገነዘበው፣ ሕፃናትና ልጆች በኮሮና ቫይረስ ተይዘው እንደ አዋቂዎች ምንም የሕመም ስሜቶች ወይም ቀላል የሕመም ስሜቶች ሊያጋጥማቸውችልም ወደ ፅኑሙማን ክፍል የመግባታቸውድል ግን ዝቅ ያለ ነው፡፡

በብሔራዊ የኅብረተሰብ ጤና አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከል የኮቪድ-19 የሕክምና አገልግሎት ተቋማት ዝግጅትና የቤት ውስጥ ራስን ለይቶ ሕክምና (ውሸባ) እንክብካቤ ክፍል ኃላፊ አቶኖክ ኃይሉ አገላለጽ፣ የኮሮና ቫይረስ ከጨቅላ ሕፃናት ጀምሮ የሚይዝ በሽታ ሲሆንፃናቱ ምንምይነት የሕመም ምልክት ላያሳዩ ወይም ቀለል ያለ የሕመም ምልክቶች ሊኖራቸው ቢችልም ወደ ሌላው የማኅበረሰብ ክፍል ግን ቫይረሱን ያስተላልፋሉ፡፡

 ሕፃናት ልጆች በሽታን የመከላከል አቅማቸውን ለማጎልበት ቤተሰቦች አቅማቸው በሚችለው መጠን ለልጆቻቸው የተመጣጠነ ምግብ ቢመግቡ ተመራጭ ነው፡፡ በሌላ መልኩ ተጓዳኝመም ላለባቸው ልጆች ልዩ እንክብካቤ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡

እንደ ኃላፊው ማብራሪያ፣ ልጆች በአሁኑ ወቅ የኮሮና ቫይረስርጭትን ለመቀነስ ወደ ውጪ ወጥተው መጫወት ስለማይችሉና ወደ ትምህርት ቤት ስለማይሄዱ፣ ከጓደኞቻቸው ጋር ስለማይገናኙም ጭንቀት፣ ድብርትና የተለያዩ የባህሪ ለውጥ ሊያሳዩ ይችላል፡፡ ስለሆነም በቤት ውስጥ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ቀለል ያለ ጤንነታቸውን እንዲሁም በአጠቃላይ የሕፃናቱን ሁኔታ ያገናዘበ የቤት ውስጥራዎችን በመሥራት፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ፣ የተመጣጠኑ ምግቦችን በመመገብ ይኼን ጊዜ ማሳለፍ አለባቸው፡፡

የተለየ የሕመም ስሜት እንደ ሳል ትኩሳት፣ የአየር ማጠር፣ ቶሎ ቶሎ የመተንፈስና ሌሎች የበሽታ ምልክቶች ከታየባቸው ወደ ጤና ተቋማት መውሰድና አስፈላጊውን የሕክምናርዳታ እንዲያገኙ ማድረግ ተገቢ ነው፡፡

ልብ ይበሉ!

የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል በምናደርገው ጥንቃቄ ለልጆቻችን የሚያስፈልጉ የሕክምና ክትትሎችን መዘንጋት ተጨማሪ የጤና እክል እንደሚያስከትሉ አንዘንጋ፡፡ ስለሆነምፃናት በቂ የቀጥታ የፀሐይ ብርሃን እንዲያገኙ ማድረግ፣ የእናት ጡት ወተት እስከ ሁለት ዓመት ድረስ (6 ወር በኋላ ከተጨማሪ ምግብ ጋር) መመገብ እንዲሁም የክትባት ጊዜያቸውን በጠበቀ መልኩና በተለያየ ጊዜ ለተላላፊ በሽታዎች ማስከተብ የሚገባውን ክትባት እንዲያገኙ ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡

‹‹በዚህ ወቅት ግዴታ ሆኖ ሕፃናት ልጆቻችንን ይዘን ከቤት ከወጣን ከሁለትመት በላይ ለሆኑፃናት የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ሳያወልቁ፣ የእጃቸውን ንፅህና እየጠበቅን ርቀታቸውን በመጠበቅ ለኮሮና ቫይረስ መስፋፋት ምክንያት ባለመሆን ራሳችንን እና ልጆቻችንን ከኮሮና ቫይረስ እንጠብቅ፡፡››

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...