Sunday, June 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናመንግሥት በሳዑዲ ዓረቢያ  በስቃይ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ወደ አገር ቤት ሊመልስ ነው

መንግሥት በሳዑዲ ዓረቢያ  በስቃይ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ወደ አገር ቤት ሊመልስ ነው

ቀን:

በሳዑዲ ዓረቢያ በእሥር ላይ የሚገኙ የኢትዮጵያ ስደተኞች በሰቆቃ ውስጥ እንደሚገኙ ቴሌግራፍ ዩኬ ሲዘግብ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ደግሞ ሁለት ሺሕ ስደተኞችን ለመመለስ ዝግጅት መደረጉን አስታውቋል፡፡

የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ነሐሴ 29 ቀን 2012 ዓ.ም. በአምባሳደሮች ዓመታዊ ስብሰባና በተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ በሰጡት መግለጫ፣ በተለያዩ አገሮች ውስጥ በችግር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ለመመለስ አቋም መያዙን አመልክተዋል፡፡

ከመስከረም 8 እስከ ጥቅምት 6 ቀን 2013 ዓ.ም. ባለው አንድ ወር ውስጥ 2000 ስደተኞች ከሳዑዲ ዓረቢያ እንደሚመለሱ ሚኒስቴሩ በመግለጫው ያስታወቀ ሲሆን፣ ከሚያዝያ እስከ ሐምሌ 2012 ዓ.ም. 3500 በስቃይ ውስጥ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ከሳዑዲ ዓረቢያ መመለሳቸውን ገልጿል፡፡

ከግንቦት 2009 ዓ.ም. እስከ መጋቢት 2012 ዓ.ም ድረስ ከ40 ሺሕ በላይ ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ፣ ባለፈው ሳምንት ነሐሴ 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ደግሞ 165 ኢትዮጵያውያን ከቤይሩት መመለሳቸውንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቢሮ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል፡፡

በሳዑዲ ዓረቢያ የሚኖሩ ዜጎችን ደኅንነትና መብት ለማስጠበቅ ከሳዑዲ ንጉሥና ከሚመለከታቸው የአገሪቱ ባለሥልጣናት እንዲሁም በሌሎች የመካከለኛው ምሥራቅና አፍሪካ ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን መብት ለማስጠበቅ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት መደረጉን አምባሳደር ዲና አስታውሰዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...