Tuesday, March 28, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትበቅድመ ማጣርያው የተሰናበቱት መቐለ 70 እንደርታ እና ፋሲል ከነማ

በቅድመ ማጣርያው የተሰናበቱት መቐለ 70 እንደርታ እና ፋሲል ከነማ

ቀን:

ለመጀመርያ ጊዜ ዘንድሮ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን የሆነው መቐለ 70 እንደርታ እና የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊው ፋሲል ከነማ በጊዜ ከአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግና ከአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ተሳትፎ ውጪ ሆነዋል። 

ሁለቱ ክለቦች በሳምንቱ መጨረሻ በመቐለና ዳሬሰላም ከተሞች ባደረጓቸው ጨዋታዎች ከቅድመ ማጣርያ ወደ አንደኛ ዙር የሚያሻግራቸውን ውጤት ማስመዘገብ አልቻሉም። በደርሶ መልስ ጨዋታዎች ከውድድር ውጭ ሆነዋል። 

ነሐሴ 19 ቀን 2011 .. በመቐለ ኢንተርናሽናል ስታዲየም የመልስ ጨዋታውን ያደረገው መቐለ 70 እንደርታ ከኢኳቶሪያል ጊኒው ካኖ ስፖርት ጋር በአንድ እኩል ተለያይቷል። ፍጹም ቅጣት ምትን ጨምሮ ያገኘውን ዕድል ወደ ውጤት መቀየር አልቻለም። ከሁለት ሳምንት በፊት ካኖ ስፖርት 21 በማሸነፉ በአጠቃላይ ውጤት 32 አሸንፎ አንደኛውን ዙር ተቀላቅሏል።

በሌላ በኩልም በኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ቅድመ ማጣርያ ከሳምንታት በፊት በባህር ዳር ኢንተርናሽናል ስታዲየም አዛም ስፖርትን 10 አሸንፎ የነበረው ፋሲል በዳሬሰላም ውጤቱን ማስጠበቅ አልቻለም። ከአዲሱ አሠልጣኙ ሥዩም ከበደ ጋር ያቀናው ክለቡ ነሐሴ 18 ቀን ከአዛም ስፖርት ጋር ባደረገው ጨዋታ 31 በመረታቱ ሩጫው ተገቷል። ለአኅጉራዊ ውድድሮች እንግዳ የሆኑት ሁለቱም ክለቦች በጊዜ የተሰናበቱት በተመሳሳይ አጠቃላይ ውጤት 32 ተረትተው ነው።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...