Tuesday, March 28, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየራባት መላ አፍሪካ ጨዋታ ዓርብ ፍጻሜውን ያገኛል

የራባት መላ አፍሪካ ጨዋታ ዓርብ ፍጻሜውን ያገኛል

ቀን:

ኢትዮጵያ በሰባት ሜዳሊያ 15 ደረጃ ይዛ ቀሪ ውድድሮችን ትጠብቃለች

ፍጻሜውን ሊያገኝ የሁለት ቀን ዕድሜ በቀረው 12ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ እስከ አሁን ሰባት ሜዳሊያዎች አስመዝግባ 15 ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ ግብጽ 94 ደቡብ አፍሪካና አስተናጋጇ ሞሮኮ 56 እና 51 ሜዳሊያዎችን በማስመዝገብ ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ይገኛሉ፡፡

በአጠቃላይ 188 አትሌቶች እያሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ድረስ፣ በካራቴ አንድ የወርቅ፣ ሁለት የብርና አራት የነሐስ በድምሩ ሰባት ሜዳሊያዎችን አስመዝግባለች፡፡ ከኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው፣ ውጤት የተመዘገበባቸው ስፖርቶች በካራቴ ታሪኩ ግርማ የወርቅ፣ ጸባኦት ጎሳዬና ሰለሞን ቱፋ የነሐስ፣ በቦክስ 52 ኪሎ ግራም ዳዊት በቀለ የነሐስ፤ በአትሌቲክስ 3,000 ሜትር መሰናክል ወንዶች ጌትነት ዋሌ የብር እንዲሁም 5,000 ሜትር ሐዊ ፈይሳና ዓለሚቱ ታሪኩ የብርና የነሐስ ሜዳሊያዎች ናቸው፡፡

ኢትዮጵያ ተጨማሪ የወርቅ፣ የብርና የነሐስ ሜዳሊያዎችን ከምታስመዘግብባቸው ውድድሮች 5,000 ሜትር የወንዶች ሩጫ ይጠበቃል፡፡ ካራቴ፣ ቅርጫት ኳስና ዋና ውድድሮች የተጠናቀቁ መሆናቸውም ታውቋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

‹‹ከኦነግ ሸኔ ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት አለን›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ

መንግሥት ከ‹‹ኦነግ ሸኔ››ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት...

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...