Tuesday, March 28, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበኢትዮጵያ የካሜሩን አምባሳደር በመኖሪያ ቤታቸው ሞተው ተገኙ

በኢትዮጵያ የካሜሩን አምባሳደር በመኖሪያ ቤታቸው ሞተው ተገኙ

ቀን:

በኢትዮጵያና በአፍሪካ ኅብረት የካሜሩን አምባሳደር የነበሩት ጃስዮ አልፍሬድ፣ ሰኞ ነሐሴ 6 ቀን 2011 ዓ.ም. በኤምባሲው መኖሪያ ቤታቸው ሞተው ተገኙ፡፡

አምባሳደሩ እ.ኤ.አ. ከ2008 ጀምረው አገራቸውን ወክለው በአምባሳደርነት በኢትዮጵያ ሲሠሩ እንደነበር ይታወቃል፡፡

ተቀማጭነታቸው ካሜሩን የሆነ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን፣ ለአምባሳደሩ ሕልፈት ምክንያት የተፈጥሮ ሕመም ሊሆን እንደሚችል ዘግበዋል፡፡

 እ.ኤ.አ. በ1957 የተወለዱት አምባሳደር አልፍሬድ አገራቸውን በተለያዩ ዘርፎች ያገለገሉ መሆናቸውን፣ ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው አስቀድሞ በአውሮፓ በተለይም በቤልጅየም በተመሳሳይ የዲፕሎማሲ ሥራ ላይ እንደነበሩ ግለ ማኅደራቸው ያሳያል፡፡

የአምባሳደሩን ድንገተኛ ሕልፈት ከተሰማ በኋላ በአዲስ አበባ የሚገኘው የካሜሩን ኤምባሲ፣ ለኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሪፖርት ማድረጉ ታውቋል፡፡

የአምባሳደሩ አስከሬን ለምርመራ ወደ ሆስፒታል መላኩን ከምንጮች ለማወቅ ተችሏል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...