Sunday, June 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ኪንና ባህል‹‹ኮቱ - ዱፌ››

‹‹ኮቱ – ዱፌ››

ቀን:

በኦሮሞ ገዳ ሥርዓት ተግባራዊ የአገር በቀል ጥበብ ላይ የሚያተኩረው የደራሲ ውብሸት ጌታሁን (ኮሎላ ደ) ‹‹ኮቱዱፌ›› በሚል ርዕስ ያዘጋጁት መጽሐፍ ለምርቃትና ለውይይት ሊበቃ ነው፡፡  ደራሲው በመግቢያው ላይ እንዳሠፈሩት፣ ‹‹በቀደምት አባቶች ተጀምሮ ዘመናትን ያስቆጠረው ወርቃማ የአስተዳደር፣ የግጭት አፈታትና የማኅበራዊ ተግባቦት ባህል በሰነድ መልክ ለማስተላለፍ እንዲቻልኮቱዱፌበመጽሐፍ መልክ ተዘጋጅቶ እንዲቀርብ ከምክንያቶቹ አንዱ የሆነው የመልካም አስተዳደርና ዴሞክራሲ ባህል በአገር ደረጃ እንዲዳብር እገዛ ለማድረግ ነው፡፡››

የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ መጽሐፉ ታኅሣሥ 15 ቀን 2011 ዓ.ም. በ10 ሰዓት በብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት ኤጀንሲ ይመረቃል፡፡

መሰንበቻውን የኅትመት ብርሃን ያየውና በኦሮሞ አገር በቀል ዕውቀት ላይ የሚያጠነጥነው መጽሐፍ ስያሜው ‹‹ኮቱዱፌ›› ትርጉም ኮቱ የሚለው በአፋን ኦሮሞ ቀጥተኛ የቃል ትርጉም እንደ ማለት ሲሆን፣ ዱፌ የሚለው ደግሞ መጣሁ እንደማለት ነው፡፡ ይሁንም እንጂ በዚህ መጽሐፉ አገባብ በቀረበበት ሁኔታ ግን ኮቱዱፌ ማለት ‹‹ስማሰማሁ›› የሚለውን የመጠራራት በሐሳብ የመቀራረብ፣ የመጠያየቅ፣ የመወያየትና የመመካከር ጥልቅ የመግባባት ትርጉም እንደሚይዝ ደራሲው ገልጸዋል፡፡

ኮቱ ዱፌ በስድስት ክፍሎች የተከፈለ ሲሆን እነሱም የአገር በቀል ዕውቀት ሥርዓት ማብራሪያዎች፣ የአባ ገዳ ሥርዓት መዋቅርና አሠራር ማሳያ፣ የገዳ ሥርዓትና ሕግጋት፣ የኮቱ ዱፌ (ስማሰማሁ) ተሳትፎ መስፈርቶች፣ በምርመራ ለመታየት የሚበቁ የኮቱ ዱፌ ሥርዓት የግጭት ደረጃዎች ናቸው፡፡ አባሪዎችና ተጨማሪ መረጃዎች በመጨረሻው ክፍል ተካትተዋል፡፡ የመጽሐፉ ዋጋ 91 ብር ነው፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...