በአፍሪካ ሰላም፣ አካባቢያዊ ልማትና ብልፅግና ላይ አጋርነትን ለማሳየት በየዓመቱ በሚካሄደው በጂቡቲ አርታ የእግር ጉዞ ላይ ኢትዮጵያ ተሳትፋለች፡፡ ኅዳር 21 ቀን 2011 ዓ.ም. ‹‹የአፍሪካ የሰላም ጉዞ›› በሚል መሪ ቃል ለ12ኛ ጊዜ በአርታ በተካሄደው የእግር ጉዞ ጂቡቲን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካና የተለያዩ የዓለም አገሮች ተሳትፈውበታል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት እንዳስታወቀው፣ 15 ኪሎ ሜትር በሸፈነው የእግር ጉዞ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የያዙ በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሠራተኞች፣ በጂቡቲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የኢትዮጵያ ወዳጆች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ እንደመግለጫው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሰላምና ልማት ላይ ቁልፍ ሚና ያላት ሲሆን በተመድ የዓለም የሰላም አስከባሪ ኃይሎች ዜጎቿን በማሰለፍ የመጀመሪያ ደረጃ መያዟ ይታወቃል፡፡
- Advertisement -
- Advertisement -
- Advertisement -
ፌርማታ ፅሁፎች
ትኩስ ፅሁፎች
- Advertisement -
- Advertisement -