Friday, March 31, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊበ50 ሺሕ ብር ዋስ ይፈቱ የተባሉት መምህር ግርማ ይግባኝ ተጠየቀባቸው

በ50 ሺሕ ብር ዋስ ይፈቱ የተባሉት መምህር ግርማ ይግባኝ ተጠየቀባቸው

ቀን:

– በተጠረጠሩበት ሐሰተኛ ሰነድ መጠቀም ወንጀል ተጨማሪ ጊዜ ተጠየቀባቸው

የእሳቸው ተከታይና የሚሏቸውን ነገር ሁሉ ያደርጉ የነበሩን ግለሰብ ቤት በማሸጥና ገንዘቡንም እንዲፀለይበት በማለት ወስደዋል ተብለው ተጠርጥረው የታሰሩት መምህር ግርማ ወንድሙ፣ በ50,000 ብር ዋስ እንዲለቀቁ ፍርድ ቤት በሰጠው ትዕዛዝ ላይ ፖሊስ ይግባኝ ማለቱ ታወቀ፡፡

የፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ወንጀል ችሎት ለመምህር ግርማ የፈቀደውን የ50,000 ብር ዋስትና የተቃወመው ፖሊስ፣ ቅሬታውን ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ወንጀል ችሎት አቅርቧል፡፡ ፖሊስ ባቀረበው መከራከሪያ ነጥብ ላይ ብይን ለመስጠት ፍርድ ቤቱ ለኅዳር 13 ቀን 2008 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ተጠርጣሪው ሐሰተኛ ሰነድ መጠቀማቸውን ገልጾ ፖሊስ ባቀረበው ክስ ምክንያት መምህር ግርማ ኅዳር 3 ቀን 2008 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርበው የነበረ ሲሆን፣ እሳቸው ከቤተክህነት እንደተሰጣቸው የገለጹት ሰነድ በፎረንሲክ ተመርምሮ ሐሰተኛ መሆኑን እንዳረጋገጠ ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ ሌላ ተጨማሪ የሚመረመር ሰነድ እንዳለውና ተጨማሪ ሰነድ ሰጥተዋል የተባሉት የቤተ ክርስቲያን አባት በአገር ውስጥ አለመኖራቸውን በማስታወቅ፣ ተጨማሪ 14 ቀናት እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡

የመምህር ግርማ ጠበቆች ፖሊስ ያቀረበውን ማመልከቻና ተጨማሪ ቀናት በመቃወም፣ ደንበኛቸው በዋስ ተለቀው ጉዳያቸውን በውጭ ሆነው እንዲከታተሉ ጠይቀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ የጠበቆቹን ማመልከቻ በማለፍ የሰባት ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ለፖሊስ ፈቅዷል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...