Thursday, March 23, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንደሌሉ አስተዳደሩ ገለጸ

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንደሌሉ አስተዳደሩ ገለጸ

ቀን:

– ተከሳሾቹ እሳቸው የማይቀርቡ ከሆነ ብይን ይሰጠን አሉ

      በተደጋጋሚ ለሦስት ጊዜያት በተጠሩበት የመከላከያ ምስክርነት ያልቀረቡበትን ምክንያት ለጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓም. እንዲያቀርብ የታዘዘው የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር፣ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንደሌሉ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት በላከው ደብዳቤ አስታወቀ፡፡

በእነ ዘመነ ካሴ የክስ መዝገብ የተከሰሱት አቶ አሸናፊ አካሉ፣ አቶ ደህናሁን ቤዛ፣ አቶ ምንዳዬ ጥላሁንና አቶ አንሙት የኔዋስ፣ አቶ አንዳርጋቸውን በመከላከያ ምስክርነት እንደሚፈልጓቸው ለፍርድ ቤት አመልክተው ነበር፡፡ ከየመን በኢትዮጵያ የፀጥታ ኃይሎች ተይዘው መምጣታቸውን በመጠቆም፣ ዋናው ክሳቸው በኤርትራ ከእሳቸው ጋር በመገናኘት መመርያና ትዕዛዝ ስለመቀበላቸው መሆኑን አስታውሰው እንዲያስረዱላቸው መጠየቃቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ሆኖም ግን ዓቃቤ ሕግ አቶ አንዳርጋቸው የዕድሜ ልክ እስራትና ሞት የተፈረደባቸው በመሆኑ፣ ቀርበው ሊመሰክሩ አይገባም በማለት ተቃውሞ ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱም የዓቃቤ ሕግን ተቃውሞ ውድቅ በማድረግ ጥያቄውን ተቀብሎ ለማረሚያ ቤቱ ትዕዛዝ አስተላልፎ ነበር፡፡

ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. አቶ አንዳርጋቸው ይቀርባሉ ተብሎ የነበረ ቢሆንም፣ ማረሚያ ቤቱ በላከው ደብዳቤ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት አለመኖራቸውን በመግለጹ ተከሳሾቹ ብሶታቸውን ገልጸዋል፡፡ ማረሚያ ቤቱ ቀደም ያሉት ትዕዛዞች በትክክለኛ አድራሻ እንዳልተጻፉለት በመግለጽ ሲያመላልሳቸው ከርሞ፣ መጨረሻ ላይ እንደሌሉ መግለጹ ተገቢ አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡ ክሳቸውን መከላከል ከጀመሩ ከአንድ ዓመት በላይ ማስቆጠራቸውንና በማረሚያ ቤት በደል እየደረሰባቸው ከመሆኑ አንፃር የአስተዳደሩ መልስ የማይታመን መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የዕድሜ ልክና የሞት ፍርደኛ ከማረሚያ ቤት ውጪ ሊታሰር እንደማይችል የገለጹት ተከሳሾቹ፣ አቶ አንዳርጋቸው ከየመን ተይዘው እንደመጡ የፀረ ሽብር ግብረ ኃይልና ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቴሌቪዥን መናገራቸውን በመጥቀስ በወቅቱ ለሁለቱም አካላት ደብዳቤ እንዲጻፍላቸው ለፍርድ ቤቱ ማመልከታቸውን አስታውሰዋል፡፡ አቶ አንዳርጋቸው በመከላከያ ምስክርነት እንዳይሰሙ ማረሚያ ቤት ችግር እየፈጠረባቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም የእሳቸው ምስክርነት ቀርቶ ብይን እንዲጣቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡

ተከሳሽ ምንዳዬ ጥላሁን የተባለው ተጠርጣሪ ግን፣ ‹‹ከአቶ አንዳርጋቸው ጋር ተገናኝተህ መመርያ ተቀብለሀል ስለተባልኩ ቀርበው መመስከር አለባቸው፤›› በማለት እንዲቀርቡ ትዕዛዝ እንዲሰጥለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡

ፍርድ ቤቱ የተከሳሾቹን አቤቱታ ካዳመጠ በኋላ አቶ አንዳርጋቸው ይገኙበታል ለተባለው ተቋም ትዕዛዝ ለመስጠት፣ ለጥቅምት 23 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...