Tuesday, March 28, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናያለመከሰስ መብታቸው ሳይነሳ የታሰሩት የምክር ቤት አባል ጉዳይ አከራከረ

ያለመከሰስ መብታቸው ሳይነሳ የታሰሩት የምክር ቤት አባል ጉዳይ አከራከረ

ቀን:

ከስምንት ወራት በፊት በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩት የጋምቤላ ክልል ምክር ቤትና ክልሉን በመወከል የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባል የነበሩት አቶ አሽኔ አስቲን ቲቶይክ በእስር ላይ የሚገኙት፣ ያለመታሰር ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው ተጥሶ መሆኑ በፍርድ ቤት አከራከረ፡፡

የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ነሐሴ 29 ቀን 2007 ዓ.ም. ጽፎ ያቀረበውን ክስ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ጥቅምት 11 ቀን 2008 ዓ.ም. ለተከሳሹ በንባብ ሊያሰማ የነበረ ቢሆንም፣ ጠበቃቸው አቶ አመሐ መኮንን ተቃውመዋል፡፡ ጠበቃው ተቃውሞአቸውን በሚመለከት ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት፣ ደንበኛቸው አቶ አሽኔ አስቲን ቲቶይክ ላለፉት ስምንት ወራት በእስር ላይ የሚገኙት የጋምቤላ ክልል ምክር ቤትና ክልሉን በመወከል የፌዴሬሽን ምክር ቤት እንደሆኑና ያለመከሰስ መብታቸው ሳይነሳ ነው፡፡

የክልሉ ሕገ መንግሥትም ሆነ የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት የምክር ቤት ተመራጭ ወንጀል ሲፈጽም እጅ ከፍንጅ ካልተያዘ በስተቀር ሊከሰስም ሆነ ሊታሰር እንደማይችል ደንግጎ ሳለ፣ ደንበኛቸው ታስረው መክረማቸው ሕገ መንግሥቱን መጣስ መሆኑን ጠበቃው አስረድተዋል፡፡ የተሰጣቸውን የምክር ቤት አባልነት መታወቂያም አለመመለሳቸውን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም በዕለቱ እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡

ከሳሽ ዓቃቤ ሕግ በበኩሉ እንዳስረዳው፣ ተከሳሹ የምክር ቤት አባል መሆናቸው እርግጥ ቢሆንም አሁን ግን የምክር ቤት አባል አለመሆናቸውን ገልጿል፡፡ የምክር ቤት አባልነት መታወቂያ የወሰዱትም በ2003 ዓ.ም. መሆኑን ጠቅሶ ጊዜው ማለፉን አስረድቷል፡፡ አባል ስላለመሆናቸውም ማስረጃ ማቅረብ እንደሚችል ለፍርድ ቤቱ ገልጿል፡፡ ፍርድ ቤቱም የዓቃቤ ሕግን ማስረጃ ለመጠባበቅ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

አቶ አሽኔ አስቲን ቲቶይክ፣ አቶ አሞት አጉዋ አኳሞይና አቶ ጀማል ዑመር የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 7(2)ን በመተላለፍ የጋምቤላ ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ (ጋሕነን) ቡድን ውስጥ መሥራችና አባል በመሆን፣ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለማፈራረስና የጋምቤላ ክልልን ከፌዴሬሽን ለመገንጠል ሲቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል በሚል ክስ እንደተመሠረተባቸው መዘገባችን ይታወሳል፡፡ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ቡድኑ ኬንያ ናይሮቢ በሚያደርገው ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ሊሄዱ ሲሉ መጋቢት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እንደነበረ መዘገቡ አይዘነጋም፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

‹‹ከኦነግ ሸኔ ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት አለን›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ

መንግሥት ከ‹‹ኦነግ ሸኔ››ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት...

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...