Friday, March 31, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበክልል ፀረ ሙስና ኮሚሽኖች ላይ ባለሥልጣናት ጣልቃ እንደሚገቡ ተጠቆመ

በክልል ፀረ ሙስና ኮሚሽኖች ላይ ባለሥልጣናት ጣልቃ እንደሚገቡ ተጠቆመ

ቀን:

በክልል የመንግሥት ተቋማትና ሕዝብ ላይ የሚፈጸም ሙስናን ለመከላከል የተቋቋሙ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽኖች፣ የክልል ባለሥልጣናት ጣልቃ በመግባት ለሥራቸው እንቅፋት እንደሚሆኑ ተገለጸ፡፡

የአገር አቀፍ የፀረ ሙስና ጥምረት የሁለት በጀት ዓመት (የ2006 እና 2007) የፀረ ሙስና እንቅስቃሴን አስመልክቶ በሸራተን አዲስ መስከረም 26 ቀን 2008 ዓ.ም. በተደረገው ውይይት እንደተገለጸው፣ የክልሎች የሥነ ምግባረና ፀረ ሙስና ኮሚሽኖች ከፌዴራሉ የተለየ የሥራ አፈጻጸም እንዳለቸው ተነግሯል፡፡

የፌደራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዓሊ ሱሌይማን እንደተናገሩት፣ የፌዴራሉ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የሚከታተላቸው ትልልቅና ግዙፍ የሕዝብ ሀብትን የሚያንቀሳቅሱ ድርጅቶችን ነው፡፡ በእነሱ ላይ ችግር ሲያጋጥም ኮሚሽኑ ለሚወስደው ዕርምጃ በትልልቅ ባለሥልጣናት ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል፡፡ አፈጻጸሙ ጥሩ ሲሆንም የማበረታታት ሁኔታዎች መኖራቸውን፣ ነገር ግን ክልሎች ተፅዕኖ አለባቸው ሲሉ ገልጸዋል፡፡ ባለሥልጣናት ጣልቃ እየገቡ የምርመራ ሒደቶችን እንደሚያስቀሩም ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ባለፈ የጣልቃ ገብነቱን ዓይነትና ዝርዝር ከመግለጽ ተቆጥበዋል፡፡

በፌዴራል በኩል ባለፉት ሁለት የበጀት ዓመታት በርካታ የሕዝብና የመንግሥት ንብረቶችን ማስመለስ መቻሉን፣ በሙሰኞች ተወስደው የነበሩ ንብረቶች መመለሳቸውንና በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ መሰብሰብ መቻሉን አስረድተዋል፡፡

ሙስናን ለመከላከል የሚበተኑ ፖስተሮች፣ በመገናኛ ብዙኃን የሚነገሩና የሚታዩ ፖስተሮችና ድራማዎች ከማስተማር ባለፈ በተቃራኒው መልዕክት ስለማስተላለፋቸው የተነሳውን ጥያቄ ኮሚሽነር ዓሊ አልፈውታል፡፡

በውይይቱ ላይ በቅርቡ በሚኒስትር ማዕረግ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሆነው የተሾሙትና የጥምረቱ ሰብሳቢ አቶ አስመላሽ ወልደ ሥላሴን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት የተገኙ ሲሆን፣ ሙስናን ለመከላከል በተለይ በምርመራ ጋዜጠኝነት ዙሪያ ቢሠራ የተሻለ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በተለይ በአሁኑ ጊዜ በሕክምና ተቋማት ውስጥ ከፍተኛ ሙስና እየተፈጸመ መሆኑን አስተያየት ሰጪዎች ቢገልጹም፣ ማብራርያ ሳይሰጥበት በዝምታ ታልፏል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...