Friday, March 31, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናለብይን ተቀጥረው የነበሩት ጦማሪያን ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ

ለብይን ተቀጥረው የነበሩት ጦማሪያን ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ

ቀን:

በተጠረጠሩበት የሽብርተኝነት ድርጊት ወንጀል ለብይን ለመስከረም 27  ቀን 2008 ዓ.ም. ተቀጥረው የነበሩት ጦማሪያን ናትናኤል ፈለቀ፣ አጥናፉ ብርሃኔ፣ አቤል ዋበላና በፈቃዱ ኃይሉ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ፡፡

ጦማሪያኑ ፍርድ ቤት ያልቀረቡበት ምክንያት ደግሞ በዕለቱ በሌላ ሥራ ምክንያት ይሁን ወይም በሌላ ጉዳይ ባይታወቅም፣ ለብይን የቀጠሯቸው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ዳኞች እንደሌሉ ተነግሯቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

ብይኑ በዕለቱ እንደሚሰጥ የገመቱ የጦማሪያኑ ቤተሰቦች፣ ጓደኞቻቸውና ጋዜጠኞች በፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ የተገኙ ቢሆንም፣ የፍርድ ቤቱ ሠራተኞች ‹‹ዳኞች ስለሌሉ እንዳይመጡ መስከረም 26 ቀን 2008 ዓ.ም. ለማረሚያ ቤቱ ተደውሎ ተነግሮታል›› በማለታቸው ለመከታተል የሄዱ ታዳሚዎች ተመልሰዋል፡፡

የጦማሪያኑ ጠበቆች ግን በሁኔታው ማዘናቸውን ተናግረዋል፡፡ ቢያንስ ቢያንስ ፍርድ ቤቱ በማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ ማስታወቂያ መለጠፍና ጉዳዩን የሚከታተሉ እንዲረዱ ማድረግ ሲገባው፣ ምንም ሳይል መሄዱ አግባብ አለመሆኑንና ታይቶም እንደማይታወቅ ገልጸዋል፡፡

ጦማሪያኑ እንዲከላከሉ ወይም መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ የሚሰናበቱበት ብይን ጥቅምት 5 ቀን 2008 ዓ.ም. ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች በሙሉ ከመስከረም 26 ቀን እስከ 30 ቀን 2008 ዓ.ም. አዳማ ሥልጠና ላይ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...