Tuesday, March 28, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊከኤርፖርቶች ድርጅት መጠኑ ያልታወቀ ገንዘብ በመዝረፍ የተጠረጠረ ሠራተኛ ተያዘ

ከኤርፖርቶች ድርጅት መጠኑ ያልታወቀ ገንዘብ በመዝረፍ የተጠረጠረ ሠራተኛ ተያዘ

ቀን:

ከኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት ዋና መሥሪያ ቤት መጠኑ ያልታወቀ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ዘርፎ ለመሰወር የሞከረው የድርጀቱ ሠራተኛ በቁጥጥር ሥር ዋለ፡፡

በኤርፖርቶች ድርጅት የሰው ኃይል አስተዳደር መምርያ የፔሮል ሠራተኛ መሆኑ የተገለጸው ተጠርጣሪ አቶ ጌታቸው ደበበ ድርጊቱን ፈጽሞ የተሰወረው ጳጉሜን 5 ቀን 2007 ዓ.ም. እንደነበር፣ የኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ኃላፊው አቶ ወንድም ተክሉ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

ተጠርጣሪው መቼ በቁጥጥር ሥር እንደዋለ፣ ምን ያህል ገንዘብ እንደወሰደና ተጨማሪ ተጠርጣሪዎች ስለመኖራቸው እንዲያስረዱ የተጠየቁት አቶ ወንድም፣ ‹‹ጉዳዩ በምርመራ ሒደት ላይ ያለ በመሆኑ ዝርዝሩን መናገር አልችልም፡፡ ድርጊቱ ግን ተፈጽሟል፡፡ ከዚህ በላይ መናገር አልችልም፤›› በማለት ዝርዝር ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡

የሪፖርተር ምንጮች እንደገለጹት ግን ተጠርጣሪው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ይዞ ለጊዜው ተሰውሮ ነበር፡፡ የገንዘቡ መጠን እንዳይታወቅ የኤርፖርቶች ድርጅት ኃላፊዎች ጉዳዩን በሚስጥር መያዛቸውንና የፋይናንስ ክፍሉ በጥብቅ ጥበቃ ላይ መክረሙንም አክለዋል፡፡

ተጠርጣሪው ድርጊቱን ብቻውን እንዳልፈጸመው ጥርጣሬ እንዳላቸው የገለጹት ምንጮች፣ በቁጥጥር ሥር ሲውል በእጁ ላይ ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ሳይገኝ እንዳልቀረም ተናግረዋል፡፡ አቶ ወንድም ተጠርጣሪው የወሰደውን ገንዘብ ሳያጠፋ ሙሉ በሙሉ መያዙን ጠቁመዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

‹‹ከኦነግ ሸኔ ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት አለን›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ

መንግሥት ከ‹‹ኦነግ ሸኔ››ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት...

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...