Friday, March 31, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየሰማያዊ ፓርቲ አመራር የነበሩ ተጠርጣሪዎች ግንቦት ሰባትን ለመቀላቀል መሄዳቸውን አመኑ

የሰማያዊ ፓርቲ አመራር የነበሩ ተጠርጣሪዎች ግንቦት ሰባትን ለመቀላቀል መሄዳቸውን አመኑ

ቀን:

–  ‹‹በደረሰብኝ በደል ወደ አርበኞች ግንባር ገብቻለሁ››

ሰላማዊ ትግል የማያዋጣ በመሆኑ ከግንቦት ሰባትና አርበኞች ግንባር ጋር በመቀላቀል መንግሥትን በትጥቅ ትግል መገልበጥ እንዳለባቸው በማመን ወደ ኤርትራ ሊሻገሩ ሲሉ፣ የካቲት 18 ቀን 2007 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር ውለዋል የተባሉት የሰማያዊ ፓርቲ አመራር የነበሩ አራት ተጠርጣሪዎች፣ ግንቦት ሰባትን ለመቀላቀል እየሄዱ እንደነበር ለፍርድ ቤት የእምነት ቃላቸውን ሰጡ፡፡

በሰማያዊ ፓርቲ ውስጥ የተለያየ ኃላፊነት የነበራቸው ተከሳሾቹ ብርሃኑ ተክለያሬድ፣ እየሩሳሌም ተስፋ፣ ፍቅረማርያም አስማማውና የአርበኞች ግንባር አባል መሆኑን የገለጸው ደሴ ካሳዬ ሲሆኑ፣ የእምነት ክህደት ቃላቸውን የሰጡት ጉዳዩን እየመረመረው ለሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 14ኛ ወንጀል ችሎት ነሐሴ 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ነው፡፡

ሁሉም ተከሳሾች ድርጊቱን መፈጸማቸውን ነገር ግን ጥፋተኛ አለመሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ብርሃኑ ለፍርድ ቤቱ እንደተናገረው፣ ‹‹አገሬ ጨቋኝ ሥርዓት ውስጥ ስላለች ይኼንን ለመታገል ግንቦት ሰባት ከተባለ ነፃ አውጭ ድርጅት ጋር ለመገናኘት ጉዞ ጀምሬያለሁ፡፡ ስለዚህ ድርጊቱን ፈጽሜያለሁ፡፡ ግን ጥፋተኛ አይደለሁም፤›› ብሏል፡፡

ኢየሩሳሌምም ድርጊቱን መፈጸሟን አምና ጥፋተኛ አለመሆኗን ገልጻለች፡፡ ሦስተኛው ተከሳሽ ፍቅረ ማርያም ደግሞ ዴሞክራሲ ለማስፈን ድርጊቱን መፈጸሙን ገልጾ፣ ጥፋተኛ አለመሆኑን አስረድቷል፡፡

ትግሪኛ እንጂ አማርኛ እንደማይሰማ የገለጸው አራተኛ ተከሳሽ ችሎቱ አስተርጓሚ እንዲቀርብለት ካደረገ በኋላ በሰጠው የእምነት ቃል፣ ‹‹በደረሰብኝ በደል ወደ አርበኞች ግንባር ገብቻለሁ፡፡ ድርጊቱን ፈጽሜያለሁ፡፡ ነገር ግን ጥፋተኛ አይደለሁም፤›› በማለት የእምነት ክህደት ቃሉን ሰጥቷል፡፡

ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ ተከሳሾቹ ድርጊቱን መፈጸማቸውን አምነው ጥፋተኛ እንዳልሆኑ በመግለጽ በመቃወማቸው ምክንያት፣ ዓቃቤ ሕግ ጥፋተኛ ስለመሆናቸው የሚያስረዱለትን ምስክሮች ነሐሴ 22 ቀን 2007 ዓ.ም. አቅርቦ እንዲያሰማ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...