Friday, March 31, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች በዓቃቤ ሕግ ላይ ያቀረቡት መቃወሚያ ውድቅ ተደረገ

የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች በዓቃቤ ሕግ ላይ ያቀረቡት መቃወሚያ ውድቅ ተደረገ

ቀን:

–  ጠበቃቸው በመታገዳቸው ያለጠበቃ ነው የቀረቡት

በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው የቀድሞ አንድነት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት)፣ የሰማያዊና የአረና ፓርቲዎች አመራሮችና ሌሎች ተከሳሾች ከሳሽ ዓቃቤ ሕግ ያቀረበባቸው የሰነድ ማስረጃዎችን ‹‹በሕጋዊ መንገድ የተገኙ ማስረጃዎች አይደሉም›› በማለት አቅርበውት የነበረው መቃወሚያ፣ ሐምሌ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. ውድቅ ተደረገ፡፡  

የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ያቀረበውን ክስ እየመረመረው የሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት፣ የተጠርጣሪ አቶ ዘለዓለም ወርቃአገኘሁ፣ የአንድነት አመራሮች የነበሩት አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ የአረና አመራር አባል አቶ አብርሃ ደስታና የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አቶ የሺዋስ አሰፋና ባህሩ ደጉ የተባሉ ተጠርጣሪ ተከሳሾች ጠበቃ አቶ ተማም አባቡልጉ ያቀረቡት የመቃወሚያ ማመልከቻን እንዳልተቀበለው ገልጿል፡፡

ዓቃቤ ሕግ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት እንዳገኘው ገልጾ ያቀረባቸው ማስረጃዎች፣ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ውለው ከታሰሩ ሦስት ወራት በኋላ የተገኙ መሆናቸውን፣ ተከሳሾቹ ለፖሊስ መረጃ የሰጡበት መንገድና ፖሊስ ማስረጃውን የያዘበት ሁኔታ አግባብነት የሌለውና ሕጋዊ ስለመሆናቸውም ያላረጋገጠ መሆኑን በመግለጽ፣ ከዓቃቤ ሕግ ማስረጃነት እንዲወጡ ወይም እንዲሰረዙ የሚል መቃወሚያ ጠበቃ ተማም ለፍርድ ቤቱ አመልክተው ነበር፡፡

ፍርድ ቤቱ የጠበቃውን መቃወሚያ ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግ፣ ተከሳሾቹ ይከላከላሉ ወይም መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ ይሰናበቱ የሚለውን ብይን ለመስጠት፣ ለነሐሴ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ተከሳሾች በጠበቃ ተማም አባቡልጉ የተወከሉ ቢሆንም፣ ጠበቃ ተማም የዲሲፕሊን ጥፋት ፈጽመዋል ተብለው በፍትሕ ሚኒስቴር የጠበቆች ዲሲፕሊን ጉባዔ ባስተላለፈው የጥፋኝነት ውሳኔ፣ ሚኒስቴሩ አንድ ዓመት ከሰባት ወር ቅጣት ስለጣለባቸው ተከሳሾቹ ያለጠበቃ ቀርበዋል፡፡  

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...