Friday, March 31, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናጦማሪ አቤል ዋበላ የእስራት ቅጣት ተፈረደበት

ጦማሪ አቤል ዋበላ የእስራት ቅጣት ተፈረደበት

ቀን:

ፍርድ ቤት በመድፈር ወንጀል ግንቦት 19 ቀን 2007 ዓ.ም. ጥፋተኛ የተባለውና በሽብር ወንጀል ተከሰው በክርክር ሒደት ላይ ከሚገኙት ጦማሪያን መካከል አንዱ የሆነው ጦማሪ አቤል ዋበላ፣ በአራት ወራት እስራት እንዲቀጣ ግንቦት 25 ቀን 2007 ዓ.ም. ፍርድ ተሰጠ፡፡

ተከሳሹ በሌሎች ቀጠሮዎች መልካም ፀባይ እንደነበረው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ጠቁሞ፣ የአራት ወራት እስራቱን በሁለት ዓመታት ገድቦለታል፡፡

ጦማሪ አቤል ጥፋተኛ የተባለው ግንቦት 19 ቀን 2007 ዓ.ም. ዓቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ላይ አዲስ ሲዲ ለፍርድ ቤቱ ሲያቀርብ፣ የቀረበው ሲዲ ‹‹የሚመለከተው ሶሊያና ሽመልስን ብቻ ነው? ወይስ እኛንም ያካትታል?›› የሚል ጥያቄ  ሲያቀርብ ፍርድ ቤቱ እንዳይናገር ሲከለክለው በመናገሩና ፍርድ ቤቱን ‹‹ራሳችሁ ሥነ ሥርዓት›› በማለት  ኃይለ ቃል ተናግሯል ተብሎ መሆኑን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...