Friday, March 31, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -

አሸንዳ

ቀን:

በሰሜን ኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ልጃገረዶች/ሴቶች በተለይ ከነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ በወገባቸው ላይ በመቀነቶቻቸው ሸብ አድርገው፣ አስረውና አሸርጠው የሚጫወቱበት ቅጠል አሸንዳ ይባላል፡፡ በ1962 ዓ.ም. የታተመው የአለቃ ደስታ ተክለወልድ ‹‹ዐዲስ ያማርኛ መዝገበ ቃላት›› አሸንዳን ሲፈታው፣ ‹‹ርጥብ ገሣ [ሣር] የትግራይ  ልጃገረዶች በበዓል ቀን ያሸርጡታል›› በማለት ይገልጸዋል፡፡ አሸንዳ በዋግ ኽምራ (ሰቆጣ) በኽምጣኛ ቋንቋ ሻደይ ሲባል፣ ፍችውም ለምለም አረንጓዴ ሣር መሆኑ ይታወሳል፡፡ ዶ/ር ከበደ ታደሰ ባዘጋጁት ‹‹Wild Flowers of Ethiopia – የኢትዮጵያ ወፍ ዘራሽ አበቦች›› መጽሐፍም፣ አሸንዳ (Torch Lily) ረዥም መስመር ቅጠልና ከጫፉ ቢጫ/ቀይ/ብርቱካንማ አበቦች ያለው በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኝ ዓመታዊ ሐመልማል (An endemic herb) ይለዋል፡፡ [ሐመልማል ለምለም ቡቃያ፣ ሣር ቅጠል እንደማለት ነው] አሸንዳ ከ2100 እስከ 4000 ሜትር ከፍታ ላይ በተዳፋትና በመንገድ ዳር ዳር ያድጋል፣ ከሚያዝያ እስከ ጥር ድረስ ያብባል፡፡
 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...