Friday, March 31, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትሐረር በ1.8 ቢሊዮን ብር ዘመናዊ ስታዲየም እየገነባች ነው

ሐረር በ1.8 ቢሊዮን ብር ዘመናዊ ስታዲየም እየገነባች ነው

ቀን:

በሐረር ከተማ ‹‹አው አባድር›› የተሰኘ ዘመናዊ ሁለገብ ስታዲየም በ1.8 ቢሊዮን ብር እየተገነባ ነው፡፡ የስታዲየሙ ዲዛይን (በፎቶው እንደሚታየው) የሐረሪ የውድ ጌጣጌጥ ማስቀመጫ ባህላዊ ሙዳይ ቅርፅ ይዞ እንደሚገነባና ባህላዊ አልባሳትን የሚወክል እንደሚሆንም ተነግሯል፡፡ እስከ 50 ሺሕ ተመልካች የሚይዘው ይህ ስታዲየም እግር ኳስን ጨምሮ ሌሎች ስፖርቶችን፣ የተለያዩ የስብሰባ አዳራሾችና የስፖርት ምርምር ማዕከሎችን ያካትታል፡፡  እንዲሁም በውስጡ እስከ 350 አልጋ የሚይዝ ሆቴል፣ ሬስቶራንት፣ የስፖርት አካዴሚ፣ 250 ሱቆች፣ ስድስት ሺሕ ያህል መኪና የሚያቆም መናኸሪያ እንደሚኖሩት ታውቋል፡፡ በአፍሮ ጽዮን ኮንስትራክሽን ተቋራጭነት እየተገነባ ያለው ይህ ስታዲየም፣  በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የሐረሪ ክልል ቤቶች ልማትና የመንግሥት ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ አስታውቋል፡፡ በታምራት ጌታቸው

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...