ቅዳሜ ጥቅምት 5 ቀን 2009 ዓ.ም. የሸራተን አዲስ ላሊበላ አዳራሽ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች በተወጣጡ ከ250 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ተሞልቶ ነበር፡፡ አንጋፋና ወጣት የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች፣ አንጋፋ የኢሕአዴግ ባለሥልጣናት፣ የንግድ ማኅበረሰቡ ተወካዮች፣ የሲቪክ ማኅበራት ተወካዮች፣ ምሁራንና ታዋቂ ግለሰቦች ተገኝተው ነበር፡፡ “የፌዴራላዊ ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ከየት ወዴት? ፈተናዎችና መልካም አጋጣሚዎች” በሚል ርዕስ ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ባዘጋጀው መድረክ ላይ፣ ለውይይት መነሻ የሚሆኑ አራት ጽሑፎች ቀርበው ነበር፡፡ በዕለቱ የመነሻ ጽሑፎችን ያቀረቡት የኢትዮጵያ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል ምክትል ኃላፊ አቶ በረከት ስምኦን፣ የኢዴፓ መሥራችና የቀድሞ ሊቀመንበር አቶ ልደቱ አያሌው፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ዶ/ር ካሳሁን ብርሃኑና የፍሊንስቶን ሆምስ ባለቤት ኢንጂነር ፀደቀ ይሁኔ ናቸው፡፡ ነአምን አሸናፊ ያጠናቀረውን የውይይቱን ዝርዝር ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡