በዓለም ከአራት ሺሕ በላይ የተለያዩ አጥቢ እንስሳት ይኖራሉ፡፡ ከአጥቢ እንስሳት ትንሿ ‹‹ሆግ ኖስትድ ባት›› (የሌሊት ወፍ ዝርያ) ስትሆን፣ ትልቁ ደግሞ ሰማያዊው ዓሳ ነባሪ ነው፡፡ ይህ ዓሳ ነባሪ 100 ፊት የሚረዝም ሲሆን ክብደቱም 150 ቶን ነው፡፡ አጥቢ እንስሳት በየብስ ወይም በውኃ ውስጥ የሚኖሩ ሲሆን የሚያመሳስሏቸው የጋራ ባህርይ አላቸው፡፡
ሳንዲያጎዙ በድረ ገጹ እንዳሰፈረው፣ አጥቢ እንስሳትን ከሚያመሳስላቸው ነገሮች አንዱ የጀርባ አጥንት ያላቸው መሆኑ ነው፡፡ ደመ ቀዝቃዛ ሲሆኑ፣ ይህም የሰውነታቸውን ሙቀት ለመቆጣጠርና በማንኛውም ዓይነት የአየር ፀባይ ውስጥ እንዲኖሩ ያግዛቸዋል፡፡
በሰውታቸው ላይ ፀጉር አላቸው፡፡ ጡት አጥቢ ሲሆኑ፣ ይህም ልጆቻቸውን እንዲያሳድጉ በተለይም የመኖርን ክህሎት እንዲያስተምሩ ዕድል ፈጥሮላቸዋል፡፡