Sunday, June 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርት32ኛው የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል አገር አቋራጭ ዛሬ ይከናወናል

32ኛው የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል አገር አቋራጭ ዛሬ ይከናወናል

ቀን:

–    ከ1,100 በላይ ብሔራዊና የክለብ አትሌቶች ይሳተፋሉ

በኢትዮጵያ አትለቲክስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት በየዓመቱ የሚካሔደው 32ኛው የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል አገር አቋራጭ የሩጫ ውድድር ዛሬ ይደረጋል፡፡ 37 ክለቦች፣ የብሔራዊ ቡድን አትሌቶች፣ ከዘጠኝ ክልሎችና ከሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በግል ከሚወዳደሩ የተውጣጡ ከ1,100 በላይ አትሌቶች ይሳተፋሉ፡፡ ፌዴሬሽኑ 405,000 ብር ለዝግጅቱ መመደቡም ታውቋል፡፡
ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ባለፈው ሐሙስ ጥር 21 ቀን 2007 ዓ.ም. በብሔራዊ ሆቴል በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ውድድሩ በ12 ኪሎ ሜትር አዋቂ ወንዶች፣ 8 ኪሎ ሜትር አዋቂ ሴቶችና ወጣት ወንዶች እንዲሁም፣ በ6 ኪሎ ሜትር ወጣት ሴቶች ይደረጋል፡፡ ለቡድንና ለግል አሸናፊዎች 125,000 ብር የገንዘብ ሽልማት ተዘጋጅቷል፡፡
የፌዴሬሽኑ የጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቢልልኝ መቆያና የቴክኒክ ዳይሬክተሩ አቶ ዱቤ ጅሎ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በሁለቱም ፆታ በአዋቂዎች ከአንደኛ እስከ አምስተኛ፣ በወጣቶች ደግሞ እስከ ስድስተኛ ደረጃ ይዘው የሚያጠናቅቁ አትሌቶች በመጪው መጋቢት መገባደጃ በቻይና በሚደረገው የዓለም አገር አቋራጭ ውድድር ላይ አገሪቱን እንደሚወክሉ ተናግረዋል፡፡ በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉት ታላላቅ የክለብ አትሌቶች ውስጥ ቦንሳ ዳዲ፣ ገነት ያለው፣ ጎይቶም ገብረሥላሴ፣ ሙክታር እንድሪስ፣ ሕይወት አያሌውና ሐጎስ ገብረሕይወት ይገኙበታል፡፡
 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...