Friday, June 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየስፖርት ቱሪዝምን እንደሚያስፋፉ የተነገረለት ውድድር በወንጪ ሐይቅ ላይ ይካሄዳል

የስፖርት ቱሪዝምን እንደሚያስፋፉ የተነገረለት ውድድር በወንጪ ሐይቅ ላይ ይካሄዳል

ቀን:

ለሦስተኛ ጊዜ በሚካሄደውና ገቢው ሙሉ ለሙሉ ለበጎ አድራጎት ሥራ ታስቦ በየዓመቱ የሚካሄደው ስፖርታዊ ውድድር ጥር 17 ቀን 2007 ዓ.ም. በወሊሶ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው ወንጪ ሐይቅ ላይ ይካሄዳል፡፡ 300 የሚደርሱ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሠራተኞችና ሌሎች ዜጎችን በሚያሳትፈው ውድድር እንደሚካፈሉ ተገልጿል፡፡ የውድድሩ አዘጋጆች እንደገለጹት፣ ውድድሩ የስፖርት ቱሪዝምን በአገሪቱ እንዲስፋፋ ከማገዝ ባለፈ ገቢውን ለተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ማዋል መቻሉ ቦታ እንደሚያሰጠው፣ ዘንድሮም የካቲት 12 ሆስፒታል ውስጥ በአዲስ መልኩ ሊገነባ ለታሰበው የሕፃናት ድንገተኛ ሕክምና ክፍል የውድድሩን ገቢ እንደሚጠቀምበት ተገልጿል፡፡ በመዝናኛ እንቅስቃሴዎችና የአካል ብቃትን በሚያሳድጉ ስፖርቶች ታጅቦ የሚካሄደው ውድድር ለአሸናፊዎቹ ሽልማት በማበርከት እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...