Friday, June 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ኪንና ባህልምሥጋና በጣይቱ ሆቴል

ምሥጋና በጣይቱ ሆቴል

ቀን:

ጥር 3 ቀን 2007 ዓ.ም. በጣይቱ ሆቴል ከደረሰው ቃጠሎ ጋር በተያያዘ ባንድም ይሁን በሌላ መንገድ ድጋፋቸውን ላሳዩ ሁሉ ለማመስገን የተዘጋጀ የኪነ ጥበብ መርሐ ግብር ሐሙስ ጥር 14፣ 2007 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ገብረፃዲቅ ሐጎስና የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ደስታ በተገኙበት በጣይቱ ሆቴል ለሕዝብ ክፍት ሆኗል፡፡ የምሥጋና ዝግጅቱን ጣይቱ ኢንተርናሽናል አርት ሴንተር፣ የኢትዮጵያ ሠዓሊያንና ቀራፂያን ማኀበርና ኬር ኢንቨንትስ ኮሙዩኒኬሽን አንድ ላይ ሆነው አዘጋጅተውታል፡፡ ዝግጅቱ ከዓርብ ጥር 15 እስከ ጥር 17፣ 2007 ዓ.ም. ከጠዋቱ አራት ሰዓት እስከ ምሽት 12 ሰዓት ለሕዝብ ክፍት ይሆናል፡፡ በመክፈቻው ዕለት 300 እንግዶች መገኘታቸውንና 400 የሚሆኑ ሥዕሎች ለዕይታ መብቃታቸውን የጣይቱ አርት ሴንተር ዳይሬክተር አቶ ዘለዓለም ግዛው ለሪፖርተር ገልጿል፡፡ በመርሐ ግብሩም 30 ሠዓሊያን፣ ገጣሚያን፣ ድምፃውያን፣ እንዲሁም ኢትዮከለር ባንድ ተሳታፊ ናቸው፡፡ በዝግጅቱ ላይ ለመሳተፍ ብዙ የኪነ ጥበብ ሰዎች ፈቃደኝነታቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ዝግጅቱ ለታዳሚ ክፍት የሆነው በነፃ ነው፡፡ በዝግጅቱ የሥዕል ዐውደ ርዕይ፣ የሙዚቃ ኮንሰርት፣ ሰርከስ፣ ግጥም፣ መዝናኛ፣ የሥዕል ሥልጠና፣ ለሕፃናት የአዝማሪ ጨዋታዎችና የጣይቱ መስተንግዶ ይኖራል፡፡ ዝግጅቱ ከምሥጋና ባሻገር ጣይቱ ሆቴል በአሁኑ ወቅትም አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ለማሳወቅ እንደሚያስችል አቶ ዘለዓለም አክሏል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...