Sunday, December 10, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ ከዊነር የስፖርት ውርርድ ተቋም ጋር የስፖንሰርሺፕ ስምምነት...

ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ ከዊነር የስፖርት ውርርድ ተቋም ጋር የስፖንሰርሺፕ ስምምነት ተፈራረመ

ቀን:

ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ ከዊነር የስፖርት ውርርድ ተቋም ጋር የስፖንሰርሺፕ የስምምነት ውል ማሰሩን አስታወቀ፡፡ ሁለቱ ተቋማት ለሦስት ዓመታት የሚቆይ የአጋርነት ስምምነት የተፈራረሙ ሲሆን፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓመት 25 ሚሊዮን ብር ያገኛል ተብሏል፡፡

ጥቅምት 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ስምምነታቸውን ይፋ ያደረጉት ሁለቱ ተቋሞች፣ ስምምነቱ በክለቡ ታሪክ ከፍተኛ ጥቅም የሚያስገኝ ስፖንሰርሺፕ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡

የዊነር ኢቲ ስፖርት ውርርድ ዋና ሥራ አስኪያጅ  ወ/ሮ ንጋት ሙሉጌታና የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማኅበር ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን በቀለ ስምምነታቸውን ፈጽመዋል፡፡

የዊነር ኢት ስፖርት ውርርድ ተቋም ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ንጋት ስምምነቱን አስመልክተው እንደተናገሩት፣ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ግዙፍ ስምና ዝና ካተረፈው ቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ለሦስት ዓመታት የሚዘልቅ የላቀ አጋርነት ስምምነት መፈራረም መቻላቸው እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል፡፡

በስምምነቱ መሠረት ተቋሙ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ለገባውና ለሦስት ዓመታት ለሚዘልቀው የላቀ አጋርነት ጥምረቱ፣ በቀዳሚው ዓመት የ25 ሚሊዮን ብር ክፍያ ይፈጽማል ተብሏል፡፡ ከዚያም የተከታዮቹ ሁለት ዓመታት ጥምረትም በክለቡና በኩባንያው መካከል በሚደረጉ ውይይቶች በሚደረስባቸው ስምምነቶች መሠረት የሚቀጥል እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡

ከዚህም ባሻገር የስፖርት ውርርድ ተቋሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስ በሦስት ዓመታት ውስጥ ከሚያቀርበው ፋይናንስ ባሻገር፣ የስፖርት ክለቡን የጨዋታና ልምምድ ትጥቆች ምርት ሙሉ ወጪ እንደሚሸፍን ገልጸዋል፡፡

ስምምነቱ የኢትዮጵያን እግር ኳስ ከመደገፍ በዘለለ፣ ተቋሙ ከፍተኛ ቁጥር ካለው የክለቡ ደጋፊ ለማስተዋወቅ አመቺ ዕድል ይፈጥራል ተብሏል፡፡

የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማኅበር ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን በቀለ በበኩላቸው እንደተናገሩት፣ ከተመሠረተ 88 ዓመታት ያስቆጠረው አንጋፋው ክለብ፣ ሁሌም ማሸነፍን ዓላማው አድርጎ የሚጫወት፣ የኢትዮጵያን እግር ኳስ በአኅጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረክ ከፍ አድርጎ ለማሳደግ የሚተጋ የሕዝብ ክለብ መሆኑን አንስተዋል፡፡

እንደ አቶ ሰለሞን ማብራሪያ፣ ስፖርት ክለቡ ከዚህ ስምምነት በታሪኩ ትልቁን የፋይናንስ ስፖንሰርሺፕ ጥቅም እንደሚያገኝ ጠቅሰው፣ ይህም ክለቡ የውስጥ አቅሙን በማሳደግ የቡድኑን ውጤታማነት ለማስቀጠል ይጠቀምበታል ብለዋል፡፡

በስምምነቱ መሠረት ቅዱስ ጊዮርጊስ በሚጠቀምባቸው የጨዋታም ይሁን የልምምድ ማሊያዎች ላይ ዓርማው በጉልህ የሚታተም ሲሆን፣ ክለቡ በሚያካሂዳቸው ማናቸውም ሁነቶች፣ የፕሬስ መግለጫዎች፣ የሕዝብ ግንኙነት መድረኮች፣ እንዲሁም የሥራ አመራሩ፣ አሠልጣኞችም ሆኑ ተጫዋቾች የሚሰጧቸው መግለጫዎች የተቋሙን ዓርማ እንዲተዋወቅ የማድረግ ኃላፊነት አለበት፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለሰው ልጅ መብት መከበር ስናወራ 75 ዓመት ሞላን!

በገነት ዓለሙ ዓለም ስለሰብዓዊ መብቶች ሲያወራ፣ ሲምል፣ ሲገዘት፣ ሲፈጠም፣ ቃል...

ካልተማከለ የካፒታል ገበያ ወደ ዘመናዊና የተደራጀ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ

በእሱፈቃድ ተረፈ በአገራችን የካፒታል ገበያ አዋጅ መውጣትን ተከትሎ የተማከለ የሰነደ...

ለማይቀረው ምክክርና ድርድር እንዘጋጅ

በያሲን ባህሩ  የዘመናዊት ኢትዮጵያ ፖለቲካ ውዝግብ በትንሹ የአንድ ምዕተ ዓመት...

ደንብ አስከባሪዎች ደንብ ያክብሩ!

በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ አስከባሪዎች፣ ሌሎች የፀጥታ አካላት፣ እንዲሁም...