Monday, December 11, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ፍሬከናፍር‹‹በመካከለኛው ምሥራቅ ዓለም አቀፍ ሰብዓዊ ሕግ በግልጽ መጣሱ በጣም ያሳስበኛል››

‹‹በመካከለኛው ምሥራቅ ዓለም አቀፍ ሰብዓዊ ሕግ በግልጽ መጣሱ በጣም ያሳስበኛል››

ቀን:

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬስ፣ የእስራኤልና የሐማስ ጦርነት በአስቸኳይ ካልቆመ በመካከለኛው ምሥራቅ ዓለም አቀፍ ሰብዓዊ ሕግ በግልጽ መጣሱ በጣም እንደሚያሳስባቸው ከተናገሩት የተወሰደ፡፡ ማንም ሰው ከዓለም አቀፍ ሰብዓዊ ሕግ የበላይ መሆን አይችልም ያሉት ጉተሬስ፣ ለሰላማዊ ሰዎች የሚደረገው ጥበቃ ከምንም ነገር በላይ መሆን ይኖርበታል ብለዋል፡፡ በጋዛ በፍልስጤም ሕፃናት ላይ እየደረሰ ያለው ፍጅትና ጉዳትም እንዲቆም በመጠየቅ፣ ‹‹ጋዛ የሕፃናት መካነ መቃብር መሆኗ ያሳስባል›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡ ሐማስ በፈጸመው የሽብር ጥቃት ያደረሰውን ጉዳት ያወገዙት ዋና ጸሐፊው፣ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ በፍጥነት ያገታቸውን ሰዎች እንዲለቅ በድጋሚ ጥሪ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል፡፡ በምንም ዓይነት ሁኔታ ሰላማዊ ሰዎችን መጉዳት፣ ማሰቃየት፣ መግደልና ማገት ፍትሐዊ ሊሆን አይችልም ብለዋል፡፡ ከመካከለኛው ምሥራቅ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከአሥር ሺሕ በላይ ፍልስጤማውያን ሲሞቱ፣ የሕፃናቱ ቁጥር ከአራት ሺሕ በላይ ሲሆን፣ በእስራኤል በኩል 1,400 ያህል ተገድለው ከ200 በላይ ሰዎች በሐማስ ታግተዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለሰው ልጅ መብት መከበር ስናወራ 75 ዓመት ሞላን!

በገነት ዓለሙ ዓለም ስለሰብዓዊ መብቶች ሲያወራ፣ ሲምል፣ ሲገዘት፣ ሲፈጠም፣ ቃል...

ካልተማከለ የካፒታል ገበያ ወደ ዘመናዊና የተደራጀ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ

በእሱፈቃድ ተረፈ በአገራችን የካፒታል ገበያ አዋጅ መውጣትን ተከትሎ የተማከለ የሰነደ...

ለማይቀረው ምክክርና ድርድር እንዘጋጅ

በያሲን ባህሩ  የዘመናዊት ኢትዮጵያ ፖለቲካ ውዝግብ በትንሹ የአንድ ምዕተ ዓመት...

ደንብ አስከባሪዎች ደንብ ያክብሩ!

በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ አስከባሪዎች፣ ሌሎች የፀጥታ አካላት፣ እንዲሁም...