Wednesday, December 6, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ፍሬከናፍር‹‹ጋዛ ውስጥ በሦስት ሳምንታት ብቻ 3,200 ያህል ሕፃናት ተገድለዋል››

‹‹ጋዛ ውስጥ በሦስት ሳምንታት ብቻ 3,200 ያህል ሕፃናት ተገድለዋል››

ቀን:

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የዕርዳታና የሥራ ኤጀንሲ ኮሚሽነር ጄኔራል ፊሊፕ ላዛሪኒ የሕፃናት አድን ድርጅት (ሴቭ ዘ ችልድረን) መረጃን ጠቅሰው፣ ለተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፡፡ ኮሚሽነር ጄኔራሉ በተጨማሪም ጋዛ ውስጥ ካለቁት ፍልስጤማውያን 70 በመቶ ያህሉ ሕፃናትና ሴቶች መሆናቸውን አክለዋል፡፡ የተመድ የሕፃናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) መረጃን ዋቢ በማድረግም በየቀኑ 420 ሕፃናት እየተገደሉ ወይም እየቆሰሉ መሆናቸውን ለፀጥታው ምክር ቤት አስረድተዋል፡፡ እስካሁን በእስራኤል ጥቃት ከስምንት ሺሕ በላይ ፍልስጤማውያን ተገድለው ከ19 ሺሕ በላይ ሲቆስሉ፣ ሐማስ በፈጸመው ጥቃት ደግሞ ከ1,400 በላይ እስራኤላውያን ተገድለው 239 መታገታቸውን ከተለያዩ የዜና አውታሮች ዘገባ ለመረዳት ተችሏል፡፡ በምሥሉ ላይ የሚታዩት ከጥቃት የተረፉ ፍልስጤማውያን ሕፃናት ናቸው፡፡ (ፎቶ አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ)

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...