Sunday, December 10, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊ‹‹ሴቶች በጦርነት ቀዳሚ ተጎጂ መሆናቸው እየታወቀ ለሰላም ስምምነት ዕድል የሚነፈጋቸው ለምንድነው?›› የኢትዮጵያ...

‹‹ሴቶች በጦርነት ቀዳሚ ተጎጂ መሆናቸው እየታወቀ ለሰላም ስምምነት ዕድል የሚነፈጋቸው ለምንድነው?›› የኢትዮጵያ ሴቶች ማኅበር ቅንጅት

ቀን:

ሴቶች በጦርነት ቀዳሚ ተጎጂዎች ቢሆኑም በሰላም የስምምነት ሒደቶች ወቅት ዕድል እንደማያገኙና ቅድሚያ እንደማይሰጣቸው የኢትዮጵያ ሴቶች ማኅበር ቅንጅት አስታወቀ፡፡

የማኅበራት ቅንጅቱ ይህንን ጥቅምት 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ከሁሉም ክልሎችና ከሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ሴቶች የሚገኙበት የሴቶችን ድምፅ ለማጉላት ያለመ ‹‹ቡና ለሰላም›› የማኅበረሰብ ውይይት ማጠቃለያ ውይይት ላይ ነው፡፡

‹‹ሴቶች በጦርነት ቀዳሚ ተጎጂ መሆናቸው እየታወቀ ለሰላም ስምምነት ዕድል የሚነፈጋቸው ለምንድነው?›› የኢትዮጵያ ሴቶች ማኅበር ቅንጅት | Ethiopian Reporter | ሪፖርተር
የቅንጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ሳባ ገብረ
መድኅን

ባለፉት አራት ዓመታት በኢትዮጵያ በተከሰቱ ግጭቶችና ጦርነቶች ሴቶች ቀዳሚ ተጎጂ መሆናቸውን፣ ይሁንና በሚደረጉ የሰላም የስምምነት ሒደቶች ላይ በበቂ ሁኔታ እየተወከሉና ድምፃቸውን እየተሰማ አለመሆኑን የቅንጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ሳባ ገብረ መድኅን አስረድተዋል፡፡

ከዚህ ቀደም የተደራጀው የኢትዮጵያ ‹‹ሴቶች ለሰላም ግንባታ›› አባላት በየወረዳው የተተገበሩ ‹‹ቡና ለሰላም›› የተሰኘ ፕሮጀክት ተቀርፆ ሲተገበር መቆየቱን ተናግረዋል፡፡

ይህ ፕሮጅከት በዋናነት በስምንት ክልሎች፣ 16 ወረዳዎች የማኅበረሰብ ውይይት የተደረገ መሆኑን የገለጹት ወ/ሮ ሳባ፣ ሴቶች ስለሰላም ማውራት እንዲጀምሩ፣ ባሉበት አካባቢ የተፈጠሩ ግጭቶችና ጦርነቶች ባደረሱት ጉዳቶችና መፍትሔዎች ላይ በሰፊው እንዲወያዩ ዕድል መስጠቱን አስረድተዋል፡፡

በዋናነት በግጭትና በጦርነት ወቅት አንደኛ ተጎጂ ሴቶች በመሆናቸው መፍትሔ ላይም መጨረሻ መሆን እንደሌለባቸው ተናግረዋል፡፡

የመንግሥት አካላት ሴቶች በየደረጃው በሰላም ውይይቶች እንዲሳተፉ ሁኔታዎችን ምቹ እንዲያደርጉና ዕድል እንዲሰጣቸው ተናግረዋል፡፡

‹‹ቡና ለሰላም›› ፕሮጀክት በተለያዩ ወረዳዎች የተሞከረ መሆኑን፣ ሴቶቹ አሁንም ጥያቄ የሚያቀርቡት የግጭትና የሰላም ዕጦት ሥጋት እንዳለባቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ቡና ለሰላም የሰላም ውይይቶች በተለያዩ ወረዳዎች የተውጣጡ እናቶች መንግሥት በየአካባቢው የሚነሱ ግጭቶችን በሰላም እንዲፈታና በችግሩ ምክንያት ለተለያዩ ችግሮች የተጋለጡ ሴቶች ትኩረት እንዲጣቸው ጠይቀዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለሰው ልጅ መብት መከበር ስናወራ 75 ዓመት ሞላን!

በገነት ዓለሙ ዓለም ስለሰብዓዊ መብቶች ሲያወራ፣ ሲምል፣ ሲገዘት፣ ሲፈጠም፣ ቃል...

ካልተማከለ የካፒታል ገበያ ወደ ዘመናዊና የተደራጀ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ

በእሱፈቃድ ተረፈ በአገራችን የካፒታል ገበያ አዋጅ መውጣትን ተከትሎ የተማከለ የሰነደ...

ለማይቀረው ምክክርና ድርድር እንዘጋጅ

በያሲን ባህሩ  የዘመናዊት ኢትዮጵያ ፖለቲካ ውዝግብ በትንሹ የአንድ ምዕተ ዓመት...

ደንብ አስከባሪዎች ደንብ ያክብሩ!

በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ አስከባሪዎች፣ ሌሎች የፀጥታ አካላት፣ እንዲሁም...