በሳይንስ ሙዚየም በተዘጋጀው ዓውደ ርዕይ የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮን ጨምሮ ክልሎች፣ ሆቴሎች፣ አስጎብኚ ድርጅቶች፣ ሬስቶራንቶች፣ ሎጆች፣ ባንኮች፣ የቴክኖሎጂ ተቋማት፣ ሚዲያዎች፣ የዕደ-ጥበብ አምራቾችና ሌሎችም ምርቶቻቸውንና አገልግሎቶቻቸውን እያስተዋወቁ ይገኛሉ፡፡ በመስከረም 29 ጀምሮ ጥቅምት 28 ቀን 2016 ዓ.ም. በሚያበቃው ኤግዚቢሽንና ሆስፒታሊቲ ዓውደ ርዕይ፣ በኢትዮጵያ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎች በቨርቹዋል ቱር የሚቃኙበት ነው፡፡
(ፎቶ፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ)