Wednesday, December 6, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናቻይና የኢትዮጵያን የቆዳ ስፋት 80 በመቶ የሚሸፍን የሳተላይት መረጃ በነፃ አቀረበች

ቻይና የኢትዮጵያን የቆዳ ስፋት 80 በመቶ የሚሸፍን የሳተላይት መረጃ በነፃ አቀረበች

ቀን:

የቻይና መንግሥት የኢትዮጵያን ሙሉ የቆዳ ስፋት የሚሸፍን የሳተላይት መረጃ በነፃ ለማቅረብ ከቻይና መንግሥት ጋር በተደረሰው ስምምነት መሠረት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያን 80 በመቶ የቆዳ ስፋት የሚሸፍን የሳተላይት መረጃ ማቅረቧን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ።

ሚኒስቴሩ የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ሦስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ሥራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ቋሚ ኮሚቴ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ባቀረበበት ወቅት እንደገለጸው፣ ከሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም. ወዲህ በተፈጠረው ትብብር አማካይነት የኢትዮጵያን ሙሉ የቆዳ ስፋት የሚሸፍን የሳተላይት መረጃ በየዓመቱ በነፃ ለማቅረብ ስምምነት ተደርሷል። በዚሁ መሠረትም በበጀቱ ዓመቱ የመጀመሪያ ሦስት ወራት የኢትዮጵያን 80 በመቶ የቆዳ ስፋት የሚሸፍን ሁለት ሜትር ‹‹ሪዞሊውሽን›› (የምስል ጥራት) ያለው የሳተላይት መረጃ በነፃ መገኘቱን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

ቻይና የኢትዮጵያን የቆዳ ስፋት 80 በመቶ የሚሸፍን የሳተላይት መረጃ በነፃ አቀረበች | Ethiopian Reporter | ሪፖርተር

የኢትዮጵያን ሙሉ የቆዳ ስፋት የሚሸፍን የሳተላይት መረጃ በየዓመቱ ለማግኘት ከቻይና መንግሥት ጋር በተገባው ስምምነት መሠረት፣ ኢትዮጵያ መረጃውን ሌላ ወገን መሸጥ አትችልም ያለው ሚኒስቴሩ፣ በዚህም ስምምነት የሚገኘው የሳተላይት መረጃ አሁን ባለው ዓለም አቀፍ የገበያ ዋጋ 2.8 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያወጣ ገልጿል። 

ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር በመተባበር ከጥቂት ዓመታት በፊት ወደ ጠፈር የላከቻቸው ሁለት የመረጃ ሳተላይቶች የአገልግሎት ጊዜያቸውን በማጠናቀቃቸው መረጃ አሰባስበው መላክ ማቆማቸውንም ሚኒስቴሩ ገልጿል።

በመሆኑም እነዚህን ሳተላይቶቹን ለማስወገድ ዝግጅት መጀመሩን የገለጸው ሚኒስቴሩ፣ ሳተላይቶቹን የማስወገድ ሥራ በህዋ ላይ የሚገኙ ሌሎች ሳተላይቶችን በማያውክና ጉዳት በማያስከትል መንገድ ከሌሎች ተባባሪ አካላት ጋር እንደሚፈጸም አስረድቷል።

በተጨማሪም አዲስ የመሬት ምልከታ ሳተላይት ለማልማትና ለማምጠቅ በ2015 ዓ.ም. ጨረታ ወጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ በቂ ተጫራች ባለመገኘቱ መሰረዙን የጠቆመው ሚኒስቴሩ፣ በቀጣዮቹ ወራት ጨረታውን በድጋሚ ለማውጣት ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጿል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...