Sunday, December 10, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትፌዴሬሽኑ የብሔራዊ ቡድን አሠልጣኝን ለመቅጠር ከጫፍ መድረሱ ተጠቆመ

ፌዴሬሽኑ የብሔራዊ ቡድን አሠልጣኝን ለመቅጠር ከጫፍ መድረሱ ተጠቆመ

ቀን:

አኅጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ጨዋታዎች ለሚጠብቀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) አዲስ አሠልጣኝ እንደሚቀጥር ታወቀ፡፡

ከሁለት ዓመታት በላይ ከዋሊያዎቹ ጋር ከቆዩት አሠልጣኝ ውበቱ አባተ ጋር በስምምነት የተለያየው ፌዴሬሽኑ፣ ብሔራዊ ቡድኑን እንዲመሩ ጊዜያዊ አሠልጣኝ መመደቡ ይታወሳል፡፡

ሆኖም ፌዴሬሽኑ ዋሊያዎቹን የሚረከብ አሠልጣኝ ሲያፈላልግ ከቆየ በኋላ፣ የኢትዮጵያ መድን እግር ኳስ ክለብ አሠልጣኝ የሆነውን ገብረ መድኅን ኃይሌ ለመቅጠር ከጫፍ መድረሱ ተሰምቷል፡፡

ዋሊያዎቹ በቀጣይ ወር ለሚጀምረው የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ለማዘጋጀት ፌዴሬሽኑ ከአሠልጣኝ ገብረ መድኅን ጋር መነጋገሩን መረጃዎች ያስረዳሉ፡፡ ዓምና ወደ ፕሪሚየር ሊግ ካደገው መድን ጋር ጥሩ ጊዜ እያሳለፈ የሚገኘውን አሠልጣኝ ገብረ መድኅን ምርጫው ማድረጉ ተወስቷል፡፡

በዚህም መሠረት አሠልጣኙ ሥራውን እንዲጀምር፣ ፌዴሬሽኑ ከክለቡ ጋር እየተወያየ እንደሚገኝ የተጠቀሰ ቢሆንም፣ አሠልጣኙ ክለቡን የመልቀቅ ፍላጎት እንደሌለው ተጠቁሟል፡፡ ስምምነቱ ካልሰመረ ፌዴሬሽኑ ‹‹ማንን ይመርጣል?›› የሚለው የሁሉም ሰው ጥያቄ ነው፡፡   

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለሰው ልጅ መብት መከበር ስናወራ 75 ዓመት ሞላን!

በገነት ዓለሙ ዓለም ስለሰብዓዊ መብቶች ሲያወራ፣ ሲምል፣ ሲገዘት፣ ሲፈጠም፣ ቃል...

ካልተማከለ የካፒታል ገበያ ወደ ዘመናዊና የተደራጀ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ

በእሱፈቃድ ተረፈ በአገራችን የካፒታል ገበያ አዋጅ መውጣትን ተከትሎ የተማከለ የሰነደ...

ለማይቀረው ምክክርና ድርድር እንዘጋጅ

በያሲን ባህሩ  የዘመናዊት ኢትዮጵያ ፖለቲካ ውዝግብ በትንሹ የአንድ ምዕተ ዓመት...

ደንብ አስከባሪዎች ደንብ ያክብሩ!

በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ አስከባሪዎች፣ ሌሎች የፀጥታ አካላት፣ እንዲሁም...