ወጣቱ የመንጃ ፈቃድ ስላወጣ መኪናቸውን መጠቀም ይችል እንደሆነ ካህን አባቱን ጠየቃቸው፡፡ “አባቱም የትምህርት ውጤትህን ካሻሻልህ፣ መጽሐፍ ቅዱስህን ካጠናህ ፀጉርህን ከተስተካከልክ በጉዳዩ ላይ ልንገጋገር እንችላለን” አሉት፡፡
ልጅየው ከወር በኋላ ነገሮችን አስተካክሎ መኪናቸውን መጠቀም ይችል እንደሆነ በድጋሚ ጠያቃቸው፡፡ ውጤትህ ተሻሽሏል መጽሐፍ ቅዱስህንም በትጋት አጥንተሃል፡፡ ሆኖም ፀጉርህን አልተቆረጥክም አሉት፡፡
‹‹አባዬ፣ ስለዚህ ጉዳይ ብዙ ሳስብ ነበረ፡፡ የሳምሶን ፀጉር ረጅም አልነበረምን? ሙሴና ኖህ እንዲሁም ኢየሱስ ረጅም ፀጉር አይደል የነበራቸው?››
‹‹እዚህ ላይ እውነት አለህ፣ ልጄ አሉ አባቱ ‹‹ነገር ግን እነዚህ የጠቀስካቸው ሁሉ የሚጓዙት በእግራቸው ነበር፡፡››
– አረፈዓይኔ ሐጐስ ‹‹የስኮትላንዳውያን ቀልዶች›› (2005)