Sunday, December 10, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየህዳሴ ግድብን ማዕከል ያደረገ አዲስ ከተማ ሊመሠረት መሆኑን የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ገለጹ

የህዳሴ ግድብን ማዕከል ያደረገ አዲስ ከተማ ሊመሠረት መሆኑን የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ገለጹ

ቀን:

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ማዕከል ያደረገ አዲስ ከተማ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ ሊመሠረት መሆኑን የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ሀብታሙ ኢተፋ (ኢንጂነር) ገለጹ፡፡

ሚኒስትሩ ለሪፖርተር እንደተናገሩት በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የታቀደው የህዳሴ ግድብ ከተማ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ቦታዎች ላይ የሚታየው ከፍተኛ የሕዝብ ብዛት የሚተነፍስበት ይሆናል። 

‹‹ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድቡ የሚፈጥረው ዕድል አዲስ ከተማ እንዲመሠረት የሚያስገድድ ነው›› ያሉት ሚኒስትሩ ሀብታሙ ኢተፋ (ኢንጂነር)፣ ለሚመሠረተው አዲስና ዘመናዊ ከተማ የሀብት ምንጭ የሚሆነው ከግድቡ ጀርባ በሚታቆረው ውኃ መሆኑን አስረድተዋል።

በግድቡ አካባቢ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪን ለማስፋፋት ምቹ መሆኑንም ሚኒስትር ሀብታሙ (ኢንጂነር) ተናግረዋል።

‹‹ከተማን ለመፍጠር ከሚያስፈልጉ ጉዳዮች አንዱ ኢነርጂ (የኤሌክትሪክ ኃይል) ነው፣ ህዳሴ ግድብ የሚያመነጨው ኢነርጂ አዲስ ከተማ ለመፍጠር ያግዛል፣ ሌላው የመጠጥ ውኃ ሲሆን በግድቡ የሚተኛውን ውኃ በማጣራት ለከተማ የሚያስፈልግ የመጠጥ ውኃ ማቅረብ ይቻላል›› ያሉት ሚኒስትሩ፣ ‹‹የግድቡ ውኃ የሚፈጥረው የቱሪዝም መዳረሻነትና በውስጡ የሚፈጠሩት ደሴቶች፣ አምስት ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የኮርቻ ግድብ የሚፈጥረው ምቹ ዕይታና መስዕብ፣ የዓሳ ሀብትና የዓሳ ምርትን የማቀነባበር ሥራ የመሳሰሉት ከተሜነት እንዲፈጠር ያስገድዳሉ። ስለዚህ ይህንን ዕድል መጠቀም የግድ ነው፤›› ብለዋል። 

በህዳሴ ግድቡ እያንዳንዳቸው ከአምስት ሔክታር በላይ ስፋት የሚኖራቸው 70 ደሴቶች የሚፈጠሩ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ አንዱና ትልቁ ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው ደሴት 2,800 ሔክታር ስፋት እንደሚኖረው መረጃዎች ያመለክታሉ።

ህዳሴ ግድቡ ሲጠናቀቅ የሚይዘው አጠቃላይ የውኃ መጠን 74 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ሲሆን፣ ይህ ውኃ ከግድቡ ጫፍ ተነስቶ ወደኋላ እስከ 246 ኪሎ ሜትር ድረስ ርዝማኔ እንደሚኖረውና፣ ግድቡ ውኃውን ጨምሮ የሚያርፍበት የቦታ ስፋት ደግሞ 1,740 ስኩዌር ኪሎ ሜትር እንደሚሆን የተመለከትናቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ።

የከተማው መመሥረት ለህዳሴ ግድቡ ከለላና ጥበቃ እንደሚሆን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ በሚፈጠረው ከተማ ማንኛውም ዜጋ ለመኖር ቢያስብ እንዲሁም ዜጎች ቦታውን እንደ ከተማ በመመልከት በከተሜነት ቢኖሩ ሕይወታቸውን በማሻሻል ኢትዮጵያን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚችሉ ተናግረዋል።

በአካባቢው ላይ ያለውን የተፈጥሮ ሀብት በአግባቡ በማገዝ ለውጥ የማምጣት ጠቀሜታ እንዳለው የገለጹት ሚኒስትሩ ለበርካታ ኢትዮጵያን የሥራ ዕድል እንደሚፈጠርም ገልጸዋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለሰው ልጅ መብት መከበር ስናወራ 75 ዓመት ሞላን!

በገነት ዓለሙ ዓለም ስለሰብዓዊ መብቶች ሲያወራ፣ ሲምል፣ ሲገዘት፣ ሲፈጠም፣ ቃል...

ካልተማከለ የካፒታል ገበያ ወደ ዘመናዊና የተደራጀ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ

በእሱፈቃድ ተረፈ በአገራችን የካፒታል ገበያ አዋጅ መውጣትን ተከትሎ የተማከለ የሰነደ...

ለማይቀረው ምክክርና ድርድር እንዘጋጅ

በያሲን ባህሩ  የዘመናዊት ኢትዮጵያ ፖለቲካ ውዝግብ በትንሹ የአንድ ምዕተ ዓመት...

ደንብ አስከባሪዎች ደንብ ያክብሩ!

በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ አስከባሪዎች፣ ሌሎች የፀጥታ አካላት፣ እንዲሁም...