Monday, December 11, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ኪንና ባህል567ቱ ወጎች

567ቱ ወጎች

ቀን:

‹‹በዚህች ‹ጠብታ እና ቅጽበት›› በተሰኘች መለስተኛ ድርሰት ውስጥ ምጥን እና ዝንቅ የሆኑ የትዝብት፣ የኩሸት፣ የተግሳፅ እና የጥያቄ ሐሳቦቼን ከምናብ ወንዜ ጨልፌ አቅርቤያለሁ፡፡ ልክ ባልትና ቤቶች በርበሬና ሽሮ ሌላውንም ቅመም በማቀናበር አሽገው ለገበያ እንዲያቀርቡ፣ እዚህች መጽሐፍ ውስጥም እንደ በርበሬ ወይም እንደ ሽሮ ለየብቻቸው በሰፊው ሊቀርቡ የሚችሉ ሐሳቦች በትዝብት ማንኪያ እየተቆነጠሩ ተቀላቅለው ይገኛሉ፡፡ ከሚዛን ልክ አልፈው እንዳያከስሩ፣ ጎለውም ኃጢያት እንዳይሆኑ ያለ ቃላት ጋጋታና ያለ ህፀፀ ሐተታ በሚገባቸው ልክ ለሆድ መጣማቸው፣ ለህሊና መሞታቸውና ከመንፈስ መስማማታቸው እየታዩ ቀርበዋል፡፡››

567ቱ ወጎች | Ethiopian Reporter | ሪፖርተር

በመግቢያው ላይ የተጻፈው ይህን ሐተታ ያቀረቡት ‹‹ጠብታ እና ቅጽበት›› በሚል ርዕስ መጽሐፍ ያሳተሙት እፁብ ድንቅ ስለሺ (ዶ/ር) ናቸው፡፡ በመጽሐፋቸው 567 አጫጭር ወጎቻቸውን አቅርበዋል፡፡

የዚህ ጽሑፍ መሠረቶች የቆሎ ተማሪነትና በኋላም የጉልምስና ጨዋታና ልዩ ልዩ ትዝብቶቻቸው መሆኑን የገለጹት ደራሲው፣ ያቀረቧቸው አሳቦች እንደ ለማኝ እንጀራ ልዩ ልዩ ናቸው ይላሉ፡፡ ‹‹ለማኝ ካንዱ ቤት የነጭ ጤፍ፣ ከሌላው ቤት የቀይ ጤፍ፣ ከሌላው ቤት ሌላ ነገር ይቀበላል፡፡ ሊጎርስ እጁን ወደ አኮፌዳው ሲሰድ የሚያገኘው ብዙ ነገር የተጠናቀረበት ጉርሻ ነው፡፡ የዓባይ ወንዝንም ብናይ ልዩ ልዩ ከሆኑ ሽጦችና ትናንሽ ገባር ወንዞች ጠብታዎች ተጠራቅመው እንደገነቡት እንረዳለን፡፡ ባንዷ የግዮን ጠብታ የብዙ ወንዞች ቀና፣ ቀለም፣ ጥራትና ድፍርስነት ሊገኝ ይችላል፡፡ በዚህች መጽሐፍም ጠብታዎች ከተለያዩ ገጠመኞች (ሸጦች) ተጉዘው፣ ባንድ ሰው ዓለም ማያ (መነጽረ ህሊና) ተዳውረው፣ በስሙር ኅብረት የማይነጥፍ የሐሳብ ወንዝ ሁነዋል ብየ አስባለሁ፣›› ብለዋል

በመጽሐፉ ያነሷቸው አሳቦች ከረዥሙ የሰው ልጅ ምድራዊ ኑሮ እንደየአጋጣሚው በተለያየ ቅጽበት የታዘቡትንና የተደነቁበትን፣ ያዩትንና ያሳዘናቸውን በየጊዜው በጋን መዝገባቸው ውስጥ አከማችተው፣ ያለማንዛዛት ባጭሩ ማቅረባቸውን ጠቁመዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለሰው ልጅ መብት መከበር ስናወራ 75 ዓመት ሞላን!

በገነት ዓለሙ ዓለም ስለሰብዓዊ መብቶች ሲያወራ፣ ሲምል፣ ሲገዘት፣ ሲፈጠም፣ ቃል...

ካልተማከለ የካፒታል ገበያ ወደ ዘመናዊና የተደራጀ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ

በእሱፈቃድ ተረፈ በአገራችን የካፒታል ገበያ አዋጅ መውጣትን ተከትሎ የተማከለ የሰነደ...

ለማይቀረው ምክክርና ድርድር እንዘጋጅ

በያሲን ባህሩ  የዘመናዊት ኢትዮጵያ ፖለቲካ ውዝግብ በትንሹ የአንድ ምዕተ ዓመት...

ደንብ አስከባሪዎች ደንብ ያክብሩ!

በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ አስከባሪዎች፣ ሌሎች የፀጥታ አካላት፣ እንዲሁም...