Wednesday, September 27, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየእንግሊዝ መንግሥት ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ከአምስት ሚሊዮን ፓውንድ በላይ ድጋፍ አደረገ

የእንግሊዝ መንግሥት ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ከአምስት ሚሊዮን ፓውንድ በላይ ድጋፍ አደረገ

ቀን:

የእንግሊዝ መንግሥት ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የ5.9 ሚሊዮን ፓውንድ ድጋፍ አበረከተ፡፡ ድጋፉ በእንግሊዝና በኔዘርላንድስ ቀይ መስቀል ማኅበራት የቴክኒክ ዕገዛ ይታከልበታል፡፡

የእንግሊዝ መንግሥት ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ከአምስት ሚሊዮን ፓውንድ በላይ ድጋፍ አደረገ | Ethiopian Reporter | ሪፖርተር
የአሥር ተሽከርካሪዎች
ድጋፍም ተደርጓል

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የማሠልጠኛ ማዕከል፣ መስከረም 3 ቀን 2015 ዓ.ም. በተከናወነው ሥነ ሥርዓት የተበረከተው ድጋፍ የሚውለው ለጤና፣ የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦትና ንፅህና አጠባባቅ ላይ ትኩረት ላደረጉ ፕሮጀክቶች ማከናወኛ ነው፡፡

ከተበረከተውም ድጋፍ ውስጥ 3.4 ሚሊዮን ፓውንድ በገንዘብ የቀረበ ሲሆን፣ ቀሪው ደግሞ ለቴክኒክ ድጋፍ እንደሚውል ታውቋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ለፕሮጀክቶቹ አገልግሎት የሚውሉ አሥር ተሽከርካሪዎችም ድጋፍ መደረጉ በኢትዮጵያ የእንግሊዝ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡

የፕሮጀክቱ ማስጀመርያ የስምምነት ሰነድም በእንግሊዝ አምባሳደር ዳረን ዌልሽና በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ፕሬዚዳንት አቶ አበራ ቶላ መካከል ተፈርሟል፡፡

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የተቋቋመው ከፋሺስት ጣሊያን ወረራ በፊት በሐምሌ 1928 ዓ.ም. ሲሆን፣ ሥራውንም የጀመረውን በጦርነቱ ለቆሰሉ የኢትዮጵያ ወታደሮችና በወረራው ጉዳት ሊደረሰባቸው ሲቪሎች ሰብዓዊ ዕርዳታ በማድረግ ነው፡፡

ማኅበሩ የዓለም ቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ ማኅበር 48ኛው አባል ለመሆን የበቃው በተመሠረተ በሦስተኛው ወር ላይ ነው፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...