Wednesday, September 27, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ እረፍት አደርጋለሁ ብለው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ቢገቡም ባለቤታቸው በፖለቲካ ወሬ ጠምደው ይዘዋቸዋል]

  • ቆይ አንቺ ምን አሳሰበሽ?
  • እንዴት አያሳስበኝም?
  • አንቺን የገጠመሽ ችግር በሌለበት ለምንድነው ስለ አገሪቱ ፖለቲካ የምትጨነቂው?
  • እኔን የገጠመኝ ችግር እንደሌለና እንደማይኖር በምን አወቅህ?
  • ባለቤትሽ የመንግሥት ሰው ሆኖ እንዴት አንችን ችግር ሊገጥምሽ ይችላል?
  • እስኪ አትቀልድ።
  • አልቀለድኩም!
  • እንዴት? አገሪቱ ችግር ውስጥ መሆኗ የእኔ ችግር አይደለም ማለት ነው?
  • እንደዚያ ማለቴ አይደለም።
  • እና ምን እያልክ ነው?
  • በቀጥታ አንቺ ጋር የሚደርስ ችግር አይኖርም ማለቴ ነው።
  • የአገሪቱ ፖለቲካ ከዛሬ ነገ ይሰክናል ብንልም አልሆነም። ሁሉ ነገር ከድጡ ወደ ማጡ እየሄደ እየተመለከትኩ ነገ ችግሩ እኔ ጋር እንደማይደርስ ምን ማረጋገጫ ይኖረኛል?
  • አይ… እንደምትይው የተፈጠረ ነገር የለም።
  • እንዴት? ችግር የለም እያልከኝ ነው?
  • ፈተና አልገጠመንም ወይም ችግር የለም አላልኩም።
  • ምን እያልክ ነው ታዲያ?
  • ፈተና ቢገጥመንም ፈተናዎችን ወደ ዕድል እየቀየርን መጓዛችን ይቀጥላል እያልኩ ነው።
  • ይህን ነገር አንተም መንግሥትም ትሉታላችሁ እንጂ አንዲት ፈተና ወደ ዕድል ተቀይራ አልተመለከትንም።
  • በእኛ በኩል፣ ማለቴ በመንግሥት በኩል ያለው ትልቁ ችግር እሱ ነው።
  • ምኑ?
  • ያጋጠሙንን ፈተናዎችን እንዴት ወደ ዕድል እየቀየርናቸው እንደሆነ የሚያሳይ መረጃ ለሕዝብ እየሰጠን አለመሆኑ በእኛ በኩል የሚስተዋል ትልቅ ክፍተት ነው።
  • እኔ ግን ከግጭት ወደ ግጭት፣ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወደ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስንገባ እንጂ ወደ ዕድል የተቀየረ ነገር አላየሁም።
  • በእኛ በኩል በቂ መረጃ እየቀረበ ባለመሆኑ አንቺም ሆንሽ ሌላው ማኅበረሰብ ዕድሎቹን ለማየት እንደተቸገረ ይታወቃል።
  • እናንተ መረጃ ካልሰጣችሁ የአገሪቱ ችግሮች ወደ ዕድል ሲቀየሩ ለማኅበረሰቡ አይታዩም ማለት ነው?
  • እንደዚያ ማለቴ ሳይሆን…
  • ወይስ ለእኛ የሚታየው ለእናንተ አይታይም?
  • እንዴት?
  • ለእኛ የሚታየው የሰው ሕይወት እያጠፋ ያለ ግጭት ከቦታ ቦታ ሲስፋፋ ነው። ለእናንተ ግን የሚታያችሁ ሌላ ነገር ይሆን?
  • ፈተናዎች አሉ ቢሆንም ፈተናዎቹን ወደ ዕድል እየቀየርናቸው ነው ወደፊት የሚገጥሙን ፈተናዎችም ወደ ዕድል ይቀየራሉ።
  • እሱ ነገር እኮ ነው የሚገርመኝ?
  • ምኑ?
  • ሰዎች እየታሠሩና እየተሰወሩ ነው።
  • ይህንንም ወደ ዕድል እንቀይረዋለን።
  • ሰዎች መታሠራቸው ሲቆም ሳይሆን ከተፈቱ በኋላ አገር ጥለው ሲሰደዱ ነው የምናየው።
  • እሱን እኮ ነው የምልሽ?
  • ምን?
  • ወደ ዕድል እየቀየርነው ነው።
  • የሰዎች መታሰርን?
  • እህ…!
  • የታል የቀየራችሁት?
  • ይኸው ራስሽ ተናገርሽው አይደል እንዴ?
  • ምን አልኩኝ?
  • የታሠሩ ሰዎች ከአገር እየወጡ ነው አላልሽም?
  • ከአገር እየተሰደዱ ነው ያልኩት።
  • ያው ነው።
  • አሃ… እንዲህ ነው ወደ ዕድል የምትቀይሩት?
  • እንደዚያ አላልኩም።
  • እና ምና እያልክ ነው?
  • ቢታሠሩም ሲፈቱ የውጭ ዕድል ይገጥማቸዋል እያልኩ ነው።
  • እህ… ታሥረው የነበሩ አንድ ተቃዋሚ ፖለቲከኛ ከአገር ከወጡ በኋላ ፖለቲካ በቃኝ ማለታቸውንስ እንዴት ነው የምታየው?
  • እንደ ዕድል!
  • አሁን ዕድል የምትሉት ምን እንደሆነ በደንብ ገብቶኛል።
  • ምኑን ነው ዕድል የምንለው?
  • ፈተናዎቹን !

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...

ማን በማን ላይ ተስፋ ይኑረው?

በአንድነት ኃይሉ ችግሮቻችንን ለይተን ካወቅን መፍትሔውንና ተስፋ የምናደርግበትን ማወቅ እንችላለን፡፡...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ለሁለት ሳምንት ያክል የፓርቲ ስብሰባ ላይ ቆይተው አመሻሹ ላይ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ባለቤታቸው በአግራሞት ተቀብለው ስለቆይታቸው ይጠይቋቸው ጀመር]

እኔ እምልክ...? ውይ... ውይ... በመጀመሪያ እንኳን በሰላም መጣህ፡፡ እሺ ...ምን ልትጠይቂኝ ነበር? ይህን ያህል ጊዜ የቆያችሁት ለስብሰባ ነው? ስብሰባ ብቻ አይደለም። ከስብሰባ ውጪ ምን ነበር? በተለያዩ መሪ ሐሳቦች የተዘጋጁ ሥልጠናዎችን...

[ክቡር ሚኒስትሩ ለሁለት ቀናት የተካሄደውን የፓርቲያቸውን የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ አጠናቀው ወደ ቢሯቸው ሲመለሱ ቢሯቸው ውስጥ አማካሪያቸው አንድ ጽሑፍ በተመስጦ እያነበበ አገኙት]

ምንድነው እንደዚህ መስጦ የያዘህ ጉዳይ? መጡ እንዴ ክቡር ሚኒስትር፣ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ያወጣውን መግለጫ እያነበብኩ ነው፡፡ ግን እኮ ፊትህ ላይ የመገረም ስሜት ይነበባል፡፡ አዎ፣ መግለጫው ላይ...

[ክቡር ሚኒስትሩ እየጠራ ያለውን ሞባይል ስልካቸውን ተመለከቱ፣ የህዳሴ ግድቡ ተደራዳሪ መሆናቸውን ሲያውቁ ስልኩን አነሱት]

ሃሎ... ጤና ይስልጥኝ ክቡር ሚኒስትር? ጤና ይስልጥልኝ ክቡር ተደራዳሪ... የጥረትዎን ፍሬ በማየትዎ እንኳን ደስ አለዎት፡፡ እንኳን አብሮ ደስ አለን፣ ምን ልታዘዝ ታዲያ? የውኃ ሙሌቱንና አጠቃላይ የግድቡን የግንባታ ሁኔታ...