Tuesday, October 3, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናከፍርድ ቤት ውሳኔ ውጪ ለሦስት ዓመታት ታስረው የሚገኙ የኦነግ አመራሮች እንዲለቀቁ ተጠየቀ

ከፍርድ ቤት ውሳኔ ውጪ ለሦስት ዓመታት ታስረው የሚገኙ የኦነግ አመራሮች እንዲለቀቁ ተጠየቀ

ቀን:

ፍርድ ቤት በነፃ ቢያሰናብታቸውም ከችሎት ውሳኔ ውጪ ለሦስት ዓመታት ታስረው የሚገኙት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አመራሮች እንዲለቀቁ ጥያቄ ቀረበ፡፡

ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅት ‹‹ሂዩማን ራይትስ ዎች›› ሰኞ ሐምሌ 17 ቀን 2015 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ ‹‹የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ሕግን ለፖለቲካ ትርፍ መሣሪያ የማድረግ ዝንባሌን ሊያስቆሙ ይገባል›› ብሏል፡፡ አብዲ ረጋሳ፣ ዳዊት አብደታ፣ ለሚ ቤኛ፣ ሚካኤል ቦረን፣ ከኔሳ አያናና ገዳ ኦልጀራ የተባሉት የኦነግ አመራሮች፣ እ.ኤ.አ. ከ2020 ጀምሮ የታሰሩ መሆናቸውንና አቶ ገዳ ጋቢሳ ደግሞ ከ2021 ጀምሮ በእስር ላይ መሆናቸውን ድርጅቱ አስታውቋል፡፡

ታሳሪዎቹ በተያዩ ጊዜያት በተደጋጋሚ ፍርድ ቤት ቢቀርቡም፣ በስተመጨረሻ ግን በቀረቡባቸው ፍርድ ቤቶች በነፃ እንዲለቀቁ እንደተወሰነላቸው፣ ይሁን እንጂ ይህን የፍርድ ቤት ውሳኔ በሚፃረር ሁኔታ ታሳሪዎቹ ሳይለቀቁ ቆይተዋል፡፡ ይህ ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለውና የሰብዓዊ መብትን የሚጥስ መሆኑን ያመለከተው ሂዩማን ራይትስ ዎች፣ ሰዎቹ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጠይቋል፡፡

ሦስቱ ታሳሪዎች ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እስከ ሰበር ሰሚ ችሎት ደርሶ እንዲፈቱ መወሰኑን፣ የኦነግ የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ‹‹ሦስቱ ታሳሪዎች ደግሞ ዓቃቤ ሕግ ክስ ያላቀረበባቸው ናቸው፡፡ አንዱ ታሳሪ ግን በዓቃቤ ሕግ አልተከሰሰም፣ ፖሊስ ምርመራ አልከፈተበትም ወይም ፍርድ ቤት አልቀረበም›› በማለት ሰዎቹ በእስር የቆዩበትን ሁኔታ አብራርተዋል፡፡

ታሳሪዎቹ ባለፉት ሦስት ዓመታት በየፖሊስ ጣቢያው እየተዘዋወሩ ታስረው መቆየታቸውን አቶ በቴ ገልጸዋል፡፡ ወደ አምስት ፖሊስ ጣቢያዎች የተዘዋወረ ታሳሪ መኖሩንም አመልክተዋል፡፡ ያለ ቤተሰብና ያለ ጠያቂ፣ በቂ ምግብና ሕክምና ሊያገኙ በማይችሉበት በፖሊስ ጣቢያ ለረዥም ጊዜ አመራሮቹ መታሰራቸው፣ እጅግ ፈታኝና አስቸጋሪ ነው ሲሉም አክለዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተመድንና ዓለም አቀፋዊ ሕግን ከእነ አሜሪካ አድራጊ ፈጣሪነት እናድን!

በገነት ዓለሙ በእኔ የተማሪነት፣ የመጀመርያ ደረጃ ተማሪነት ጊዜ፣ የመዝሙር ትምህርት...

የሰላም ዕጦትና የኢኮኖሚው መንገራገጭ አንድምታ

በንጉሥ ወዳጅነው ፍራንክ ቲስትልዌይት የተባሉ አሜሪካዊ ጸሐፊ ‹‹The Great Experiment...

ድህነት የሀብት ዕጦት ሳይሆን ያለውን በአግባቡ ለመጠቀም አለመቻል ነው

በአንድነት ኃይሉ ድህነት ላይ አልተግባባንም፡፡ ብንግባባ ኖሮ ትናንትም ምክንያት ዛሬም...