የሰው ሙያ ሦስት ዓይነት ነው፡፡ አንደኛው ማሰብን ማወቅ፣ ሁለተኛው መናገርን ማወቅ፣ ሦስተኛው መሥራትን ማወቅ፣ አብዛኞቹ ብልህ የሚባሉ ሰዎች ከእነዚህ ከሦስቱ አንደኛውን ብቻ ነው የሚይዙት ወይም መሥራት ያውቁና ትክክል ማሰብ አይችሉም ይሆናል፡፡ ስለዚህ ትክክል ካለማሰባቸው የተነሳ ደክመው የሠሩት ሥራ ሁሉ ይፈርሳል፡፡ ወይም ደግሞ ንግግር አሳማሪዎች ሐሳባቸው ብላሽ ይሆናል፡፡ ትክክል አስቦ ያሰበውን ትክክል አድርጎ በቃል፤ ወይም በጽሑፍ አስረድቶ እንዳሰበውና እንደተናገረውም አድርጎ ትክክለኛ የሚሠራ ሰው እውነት ትልቅ አዋቂ ነው ሊባል ይችላል፡፡
– ከበደ ሚካኤል ‹‹ታሪክና ምሳሌ›› (1999)