Tuesday, September 26, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየምግብ ዕርዳታ በመቆሙ በኢትዮጵያ የሚገኙ አንድ ሚሊዮን ስደተኞች ከቀለብ ውጭ ሆነዋል ተባለ

የምግብ ዕርዳታ በመቆሙ በኢትዮጵያ የሚገኙ አንድ ሚሊዮን ስደተኞች ከቀለብ ውጭ ሆነዋል ተባለ

ቀን:

የአሜሪካ መንግሥት ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) እና ተመድ በኢትዮጵያ ሲያቀርቡት የነበረውን የምግብ ዕርዳታ በጊዜያዊነት ማቆማቸውን ተከትሎ ስደተኞች ሙሉ በሙሉ ከቀለብ ውጭ ሆነዋል ተባለ፡፡

የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ እንደገለጹት ለስደተኞች ከፍተኛ ድጋፍ ያደርግ የነበረው የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት በኢትዮጵያ የሚያደርገውን ድጋፍ በማቆሙ በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢ የሚገኙ ስደተኞች ተግዳሮት ገጥሟቸዋል፡፡

ከአንድ ሳምንት በፊት ዩኤስኤአይዲ ይፋ ባደረገው መረጃ አካሄድኩት ባለው የምርመራ ውጤት ከፍተኛ መጠን ያለው የዕርዳታ ምግብ አቅርቦት ላይ ምዝበራ መፈጸሙን ጠቅሶ በኢትዮጵያ የሚያደርገውን ዕርዳታ እንዳቆመ አስታውቆ ነበር፡፡

በዚህም የተነሳ በአፍሪካ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስደተኛ በማስተናገድ በሁለተኛ ደረጃን የምትገኘው አትዮጵያ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍል በስደተኞች መጠለያ የሚገኙ ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ የውጭ አገር ስደተኞች የምግብ አቅርቦት መቋረጡ እንዳሳሰባቸው ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡

እ.ኤ.አ. በ2023 በሶማሊያ ላሳኖድ በነበረ ግጭት 91,000 ወደ እንዲሁም በቅርቡ በሱዳን በተቀሰቀሰው ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የስደተኞች ቁጥር 10,000 መድረሱን አቶ ተስፋሁን አስታውቀዋል፡፡

ከሱዳን ሸሽተው ወደ ኢትዮጵያ የገቡት ስደተኞች በሱዳን ተጠልለው የነበሩ የኤርትራ ስደተኞችና ሱዳናውያን ሲሆኑ የሱዳን ጦርነት ከቀጠለ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ስደተኞች ቁጥር አሁንም ሊጨምር ይችላል ተብሏል፡፡ ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ ያሉ ስደተኞች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን የገለጹት ተስፋሁን ተጨማሪ ፋይናንስ ማግኘት ከባድ እየሆነ በመምጣቱ ምላሽ ለመስጠት ተቸግረናል ብለዋል፡፡

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን የኢትዮጵያ ተወካይ ማማዱ ዲያን ባለዴ (ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንግሥት ለኤርትራውያን ስደተኞች የሚያደርገው ድጋፍ ይበል የሚያሰኝ መሆኑንና ይህ ድጋፍም እንዲቀጥል እንፈልጋለን ብለዋል፡፡

የተወሰኑ ኤርትራውያን በአዲስ አበባ የባንከ አካውንት እንዲከፍቱ የሚደረገው ጥረት አሁንም መቀጠሉን ጠቅሰው፣ ከጎረቤት አገሮች ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የስደተኞች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱንና የሰላም ዕጦት ካለባቸው የጎረቤት አገሮች ወደ ኢትዮጵያ ለሚገቡ ስደተኞች አሁንም ኢትዮጵያ ድንበሯን ክፍት በማድረግ ድጋፏን በቀጣይ እንድታሳይ እንፈልጋለን ብለዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የቤት ባለንብረቶች የሚከፍሉትን ዓመታዊ የንብረት ታክስ የሚተምን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በአዋጁ መሥፈርት መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የንብረት ታክስ መጠን...

እንደ ንብረት ታክስ ያሉ ወጪን የሚያስከትሉ አዋጆች ከማኅበረሰብ ጋር ምክክርን ይሻሉ!

የመንግሥትን ገቢ በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የሚታመኑት የተጨማሪ እሴት...

ለዓለምም ለኢትዮጵያም ሰላም እንታገል

በበቀለ ሹሜ ያለፉት ሁለት የዓለም ጦርነቶች በአያሌው የኃያል ነን ባይ...