Tuesday, September 26, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናብሔራዊ ባንክ ከአንድ ባንክ በስተቀር  ሌሎች ባንኮች የጥሬ ገንዘብ  እጥረት እንደሌለባቸው አስታወቀ

ብሔራዊ ባንክ ከአንድ ባንክ በስተቀር  ሌሎች ባንኮች የጥሬ ገንዘብ  እጥረት እንደሌለባቸው አስታወቀ

ቀን:

ብሔራዊ ባንክ-የፋይናንስ ዘርፉ  አቅርቦቱና ፍላጎቱ የተመጣጠነ እንዳልሆነም ተጠቁሟል

ከአንድ ባንክ በስተቀር ሌሎች ሁሉም የንግድ ባንኮች የጥሬ ገንዘብ እጥረት (ሊኪዩዲቲ)  እንደሌለባቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዢ አቶ ሰለሞን ደስታ አስታወቁ።

ምክትል ገዥው ዛሬ ለስድስተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ስካይላይት ሆቴል እየተከናወነ ባለው የምስራቅ አፍሪካ የፋይናንስ ስብሰባ(Summit”) እንደገለጹት፣ “የገንዘብ እጥረት አለ ከተባለም ሁለት ወይም አንድ ባንክ ላይ ነው” ብለዋል።
አቶ ሰለሞን የጥሬ ገንዘብ እጥረት እንዳለበት የጠቆሙትና ስሙን ለመጥቀስ ያልፈለጉት ባንክ ግን ማኔጅመንቱ ላይ ማስተካከያ  የሚፈልግ መሆኑን ተናግረዋል።

ምክትል ገዢው ምንም እንኳን የጥሬ ገንዘብ እጥረት እንደሌለ ቢናገሩም ፣ አገሪቱ ከብዙ ነገር እንደመውጣቷ፣ ብዙ የገንዘብ ፍላጎት አለ።

ስለሆነም ኢኮኖሚውን ለማንቀሳቀስ የሚያስፈልገውን ነገር በአንድ ጊዜ ማቅረብ ለኢትዮጵያ ቀላል እንደማይሆንና የፋይናንስ ዘርፉ  አቅርቦቱና ፍላጎቱ የተመጣጠነ አለመሆኑን በመግለጽ፣ ችግሩ መኖሩን አመላካች ሀሳብ ሰንዝረዋል።

የምስራቅ አፍሪካ የፋይናንስ ስብሰባ(Summit” ለስድስተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ስካይላይት ሆቴል እየተከናወነ ሲሆን፣ በጉባዔው  የተመሰረከላቸው የሂሳብ ባለሙያዎች፣ መድን ሰጪዎች፣ የፋይናን ተቋማት ባለሙያዎችና ሃላፊዎች እንዲሁም ቴክኖሎጂ አቅራቢዎች ተገኝተዋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የቤት ባለንብረቶች የሚከፍሉትን ዓመታዊ የንብረት ታክስ የሚተምን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በአዋጁ መሥፈርት መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የንብረት ታክስ መጠን...

እንደ ንብረት ታክስ ያሉ ወጪን የሚያስከትሉ አዋጆች ከማኅበረሰብ ጋር ምክክርን ይሻሉ!

የመንግሥትን ገቢ በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የሚታመኑት የተጨማሪ እሴት...

ለዓለምም ለኢትዮጵያም ሰላም እንታገል

በበቀለ ሹሜ ያለፉት ሁለት የዓለም ጦርነቶች በአያሌው የኃያል ነን ባይ...