Tuesday, September 26, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
- Advertisement -

ፌርማታ ፅሁፎች

እሱማ እኔም ነበረኝ

ትኩስ ፅሁፎች

አንድ ደጃዝማችና አንድ ቀኛዝማች ከሌሎች ሹማምንቶች ጋር በመሆን ድግስ ላይ ይበላሉ፣ ይጠጣሉ፡፡ በመካከሉ ቀኛዝማቹ ውኃ ሽንታቸውን ለመክፈል ፈልገው አሽከራቸውን መክፈያ እንዲያመጣላቸው ያዙታል፡፡

አሽከሩም በታዘዘው መሠረት መክፈያውን ይዞ ከተፍ አለ፡፡ ይሁንና ቀኛዝማች ሽንተቸውን ለመሽናት ቢፈልጉም ፈሳቸው አብሮ መጣሁ መጣሁ እያለ አላሸና አላቸው፡፡ ከዚያ አምልጦኝ ሰው ፊት ከምዋረድ ብቆይ ይሻላል በሚል፡-

‹‹በል አንሳ›› ብለው መክፈያውን ወደዛ ገፋ ከማድረጋቸው አጠገባቸው የነበሩ ጓደኛቸው (ደጃዝማቹ)፡-

‹‹አንተ እምቢ ካልህ እኔ ልሞክር›› አሉና ሽንታቸውን መሽናተ ሲጀምሩ አምልጦአቸው አንድ ሁለቴ ቷ…ቷ አደረጉ፡፡ በዚህን ጊዜ ከሚያመልጠኝ ይቅርብኝ ብለው የተቀመጡት ቀኛዘማች፡-

‹‹አዬ ደጃዝማች ሌላ ታመጣለህ ብዬ ነው እንጂ እሱማ እኔም ነበረኝ›› አሉ ይባላል፡፡

  • ካሕሣይ ገ/እግዚአብሔር፣ ‹‹ኅብረ-ብዕር›› (1998)
- Advertisement -
- Advertisement -

ተጨማሪ ለማንበብ

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች