Sunday, June 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትተስፋ የተጣለባት አዲሷ የ10 ሺሕ ሜትር አሸናፊዋ ሚዛን ዓለም

ተስፋ የተጣለባት አዲሷ የ10 ሺሕ ሜትር አሸናፊዋ ሚዛን ዓለም

ቀን:

ከሁለት ዓመት በፊት በኬንያ በተከናወነው ከ20 ዓመት በታች የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያዊቷ ሚዛን ዓለም 5,000 ሜትር ማሸነፍ ችላ ነበር፡፡ አሁን በ21 ዕድሜዋ ላይ የምትገኘው አትሌት ስለእሷ እምብዛም የሚታወቅ ነገር አልነበረም፡፡ በበርኒንግሃም የቤት ውስጥ 3,000 ሜትር ፍፃሜ ጉዳፍ ፀጋይን በመከተል ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ ግን የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው፡፡ በአንፃሩ እምብዛም ያልተወራላትና በጥቂት ውድድሮች ላይ ስኬታማ መሆን የቻለችው የነገዋ ተስፋ ሚዛን፣ እሑድ ግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም. በእንግሊዝ በተከናወነ የዓለም አኅጉራዊ የዙር የብር ደረጃ 10 ሺሕ ሜትር ውድድር 29፡59፡03 በሆነ ጊዜ በማጠናቀቅ በግል ምርጥ ሰዓቷን ከማስመዝገቧ በላይ ከ30 ደቂቃ በታች የገባች 12ኛዋ የዓለም ምርጥ ሰዓት ባለቤት መሆን ችላለች፡፡ ሚዛን ቀድሞ በ10 ሺሕ ሜትር ከነበራት የግል ምርጥ ሰዓት በሦስት ደቂቃ ማሻሻሏ ተጠቅሷል፡፡ ሌላዋ ኢትዮጵያዊት ሀዊ ፈይሳ 31፡09፡85 በመግባት አምስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...