Sunday, June 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትኬንያ ዑጋንዳና ታንዛንያ የ2027 የአፍሪካ ዋንጫ በጋራ ለማዘጋጀት ጠየቁ

ኬንያ ዑጋንዳና ታንዛንያ የ2027 የአፍሪካ ዋንጫ በጋራ ለማዘጋጀት ጠየቁ

ቀን:

ከአራት ዓመት በኋላ የሚካሄደውን የአፍሪካ አገሮች ዋንጫ (አፍኮን) ለማዘጋጀት፣ ስድስት አገሮች ለመወዳደር ፍላጎት እንዳላቸው ማስታወቃቸውን፣ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) አስታወቀ፡፡

የካፍ ኮሚዩኒኬሽን ዘርፍ በድረ ገጹ እንዳስታወቀው፣ የ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በቀረበው ጥሪ መሠረት ፍላጎታቸውን ካሳወቁ ስድስት አገሮች መካከል ሦስቱ የምሥራቅ አፍሪካ አገሮች ኬንያ፣ ዑጋንዳና ታንዛንያ በጋራ ለማዘጋጀት ጥያቄ ያቀረቡ ናቸው፡፡ ሌሎቹ አልጄርያ፣ ቦትስዋና እና ግብፅ ናቸው፡፡

አባል ማኅበራት የአዘጋጅነት ጥያቄ ካላቸው፣ ከተሟላ ሰነድ ጋር ማቅረብ የሚገባቸው የመጨረሻው ቀነ ገደብ ግንቦት 15 ቀን 2015 ዓ.ም. መሆኑን ያስታወቀው ካፍ፣ ለአዘጋጅነት ማመልከቻቸውን ባስገቡ አገሮች በመገኘት የመስክ ምልከታ የሚደረገው ከግንቦት 24 ቀን እስከ ሐምሌ 8 ቀን ድረስ መሆኑን ገልጿል፡፡

በየሁለት ዓመቱ የሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ከ33 ውድድሮቹ ሦስቱን 3ኛ፣ 6ኛ እና 10ኛውን ውድድር ያዘጋጀችው የአፍሪካ ቀንድ አገሯ ኢትዮጵያ ናት፡፡ ለ2027ቱ ዋንጫ አዘጋጅነት የሚወዳደሩት የምሥራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ አባሎቹ ኬንያ ታንዛንያና ዑጋንዳ ካሸነፉ ከቀጣናው የመጀመርያዎቹ ይሆናሉ፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...