Friday, June 2, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

  • ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል።
  • ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ ስለምትገኝ አየር መንገዱ ይህንን ለማቃለል አስተዋጽኦ ማድረግ ይኖርበታል።
  • እኛም ይህንን እንገነዘባለን ነገር ግን አብዛኛው ወጪያችን በውጭ ምንዛሪ የሚከፈል በመሆኑ ነው በሚፈለገው ልክ አስተዋጽኦ ማድረግ ያልቻልነው።
  • አቅዳችሁ ከሠራችሁ የሚጠበቅባችሁን አስተዋጽኦ ማሳካት ትችላላችሁ። ዛሬ ባትችሉም ነገ ማድረግ ይቻላል።
  • እርግጥ ነው እኛም ትልቁ ወጪያችንን ለመቀነስና ከአየር ብክለት ነፃ የሆነ በረራ ለማድረግ አቅደን በአገር ውስጥ ነዳጅ ለማምረት ዝግጅት ጀምረናል።
  • ነዳጅ ለማምረት?
  • አዎ። ከአየር ብከለት ነፃ የሆነ ነዳጅ በአገር ውስጥ ለማምረት የጥናት ዝግጅቱ አልቋል።
  • ከአየር ብከለት ነፃ የሆነ ነዳጅ እንዴት ነው የምታመርቱ?
  • ነዳጁን ለማምረት በዋነኝነት የምንጠቀመው ግብዓት መኖ ነው።
  • ምንድነው ?
  • መኖ ነው ያልኩት ክቡር ሚኒስትር።
  • መኖ ለአውሮፕላን? እየቀለዱ ነው?
  • ተረፈ ምርቱን ማለቴ ነው።
  • የአርብቶ አደሩ ከብቶች በድርቅ ምክንያት እያለቁ እንደሆነ አያውቀም?
  • ሰምቻለሁ።
  • ታዲያ ምን የተረፈ ምርት አለ። ከአርብቶ አደሩ ጋር ልትሻሙ ካልሆነ በስተቀር?
  • ከአርብቶ አደሩ የተረፈ መኖ ማለቴ አይደለም።
  • ከመኖው ውስጥ ለምግብነት የማይውለውን ነው ለመጠቀም ያሰብነው።
  • ያው ሽሚያ ነው።
  • እንደዛ አይደለም ክቡር ሚኒስትር። አንደኛ ገና ጥናት ላይ ነው። ሁለተኛ ደግሞ እራሳችን የምናመርተውን መኖ ነው የምንጠቀመው።
  • እንደዛ ነው?
  • አዎ። እንደውም ለምግብነት የሚውለውን ክፍል ለአርብቶ አደሩ ማቅረብ እንችላለን። በተጨማሪም…
  • በተጨማሪ ምን ?
  • ከአየር ብክለት ነፃ የሆነ ነዳጅ ለማምረት የምንጀምረው ፕሮጀክት ስለሆነ በዓለም አቀፍ የገንዘብ ዕርዳታና ብድር የሚተገበር ነው።
  • በውጭ ምንዛሪ ማለት ነው?
  • በትክክል። ለዚህ ተብሎ የተቋቋመ ዓለም አቀፍ የካርበን ልቀት ቅነሳ ፈንድ አለ።
  • ይኼ በጣም ድንቅ ዕቅድ ነው።
  • ይመስለኛል። ፕሮጀክቱን ይሁንታ ካገኘ ፈንዱ ነፃ ፋይናንስና ወለድ የማይከፈልበት የረዥም ጊዜ ብድር ያቀርብልናል።
  • አሁኑኑ ይጀመር። በፍጥነት ይመረት።
  • ምኑ?
  • መኖው፡፡
  • ይህ እኮ እ.ኤ.አ. በ2050 ለማሳካት የያዝነው ዕቅድ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • አሁኑኑ ይጀመር፡፡
  • እ…
  • በተጨማሪ ደግሞ…
  • በተጨማሪ ምን?
  • መንግሥት የሚከታተለው ፕሮጀክት እንደሆነ ይነገር!

 

 

 

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅን የሚተካ ረቂቅ ተዘጋጀ

ከቫት ነፃ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ገደብ ተቀመጠለት የገንዘብ ሚኒስቴር ከሃያ...

ብሔራዊ ባንክ ለጥቃቅንና አነስተኛ ብድሮች ዋስትና መስጠት ሊጀምር ነው

ኢንተርፕራይዞችን ብቻ የሚያገለግል የፋይናንስ ማዕከል ሥራ ጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...

አዋሽ ባንክ ለሁሉም ኅብረተሰብ የብድር አገልግሎት የሚያስገኙ ሁለት ክሬዲት ካርዶች ይፋ አደረገ

አዋሽ ባንክ ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች በዘመናዊ መንገድ ብድር ማስገኘት...

መንበሩ ካለመወረሱ በስተቀር መፈንቅለ ሲኖዶስ መደረጉን ቤተ ክህነት አስታወቀ

ቅዱስ ሲኖዶስ ከነገ ጀምሮ ውይይት እንደሚጀምር ተነገረ ‹‹እኛ ወታደርም ሆነ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...

የባንኮች ብድር አሰጣጥ ፍትሐዊና ብዙኃኑን ያማከለ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

ባንኮች የብድር አገልግሎታቸውን በተቻለ መጠን ፍትሐዊ፣ የብዙኃኑን ተጠቃሚነት ያማከለና...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ የነዳጅ ግብይት በዲጂታል ክፍያ መንገድ ብቻ እንዲፈጸም የተላለፈውን ውሳኔ አተገባበር ላይ ስለተነሱ ቅሬታዎች ከባልደረባቸው ጋር እየተወያዩ ነው]

ክቡር ሚኒስትር አተገባበሩ ጥሩ ቢሆንም፣ ከፍተኛ ወቀሳ እየደረሰብን ነው። ዲጂታል የግብይት ሥርዓቱን ለማስፋፋት በመጣራችን መመስገን ሲገባን እንዴት እንወቀሳለን? የሚገርመው በዲጂታል ክፍያ ላይ የተሰማሩ ኩባንያዎች ናቸው በዋነኛነት...