Monday, December 11, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናኢሠማኮ ነገ ሊያደርገው የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመከልከሉ ተሰርዟል...

ኢሠማኮ ነገ ሊያደርገው የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመከልከሉ ተሰርዟል አለ

ቀን:

_ፓሊስ የደረሰኝም ሆነ የሰማሁት ነገር የለም ብሏል

የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) በየዓመቱ ሚያዝያ 23 ቀን የሚከበረውን የዓለም የሠራተኞች ቀን (ሜይዴይ)፣ ነገ ሚያዚያ 23 ቀን 2015 ዓም በሰላማዊ ሰልፍ በመስቀል አደባባይ እንደሚከበር የተነገረና ሪፖርተር ጋዜጣም በዛሬው እትሙ የዘገበ ቢሆንም፣ ዛሬ ሚያዚያ 22 ቀን 2015 ዓም ምሽት ላይ መሰረዙ ተነግሯል።

በኢሠማኮ ፕሬዚደንት አቶ ካሣሁን ፎሎ ፊርማ ተረጋግጦ ለሪፖርተር የተላከው መግለጫ እንደሚገልጸው፣ በዓሉ በተለያዩ ዝግጅቶች ሲከበር መቆየቱ ይታወቃል። በዘንድሮው 48ኛው የሜይዴይ በዓልን በአዲስ አበባና ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶቹ በሚገኙበት በሰላማዊ ሰልፍ ለማክበር | አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቶ፣ የበዓሉን አከባበርና አጠቃላይ መርሀ-ግብር አስመልክቶ ሚያዝያ 21 ቀን 2015 ዓ.ም. ጋዜጣዊ መግለጫ በመገናኛ ብዙሀን ማስተላለፉ አስታውሷል፡፡

ነገር ግን ሚያዝያ 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በመስቀል አደባባይ በዓሉን ለማክበር የተያዘው ፕሮግራም “የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ቢሮ ስለከለከለን” ፕሮግራሙን ለመሰረዝ የተገደድን መሆኑን እየገለጽን፤ ይህንኑ መልዕክት የኢትዮጵያ ሠራተኞች እንዲያውቁት ብሏል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንም ነገ ሚያዚያ 23 ቀን 2015 ዓም ምንም የሚያውቃቸው ኩነቶችና ሰልፍ እንደሌለም አስታውቋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለሰው ልጅ መብት መከበር ስናወራ 75 ዓመት ሞላን!

በገነት ዓለሙ ዓለም ስለሰብዓዊ መብቶች ሲያወራ፣ ሲምል፣ ሲገዘት፣ ሲፈጠም፣ ቃል...

ካልተማከለ የካፒታል ገበያ ወደ ዘመናዊና የተደራጀ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ

በእሱፈቃድ ተረፈ በአገራችን የካፒታል ገበያ አዋጅ መውጣትን ተከትሎ የተማከለ የሰነደ...

ለማይቀረው ምክክርና ድርድር እንዘጋጅ

በያሲን ባህሩ  የዘመናዊት ኢትዮጵያ ፖለቲካ ውዝግብ በትንሹ የአንድ ምዕተ ዓመት...

ደንብ አስከባሪዎች ደንብ ያክብሩ!

በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ አስከባሪዎች፣ ሌሎች የፀጥታ አካላት፣ እንዲሁም...