Monday, December 11, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ኪንና ባህልየታዋቂው የአፋን ኦሮሞ ድምፃዊ ዘሪሁን ወዳጆ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ ይፈጸማል

የታዋቂው የአፋን ኦሮሞ ድምፃዊ ዘሪሁን ወዳጆ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ ይፈጸማል

ቀን:

ስለ አገር አንድነት፣ ነፃነትና እኩልነት በአፋን ኦሮሞ በማዜም የሚታወቀው ድምፃዊ ዘሪሁን ወዳጆ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ ሚያዝያ 18 ቀን 2015 ዓ.ም. በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል፡፡

ድምፃዊው ዘሪሁን ሕክምናውን ይከታተልበት በነበረው ህንድ አገር ያረፈ ሲሆን፣ አስክሬኑ ሚያዝያ 17 ቀን አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ንጋት ላይ ሲደርስ፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ የክልልና የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣኖች አቀባበል አድርገውለታል፡፡

የድምፃዊውን የሽኝት መርሐ ግብር ለማስፈጸም የተቋቋመው ኮሚቴ በሰጠው መግለጫ፣ ድምፃዊ ዘሪሁን በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትሕ እንዲኖርና ሁሉም ብሔረሰቦች በእኩልነት እንዲኖሩ በዘመኑ ሁሉ በሙያው ሲታገል እንደነበር ገልጿል፡፡

‹‹ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ዕንቁ አርቲስቶች መካከል አንዱ ነው፤›› ያለው የድምፃዊው የሙያ ባልደረባ ድምፃዊ ሰዮ ደንደና፣ ድምፃዊ ዘሪሁን ወዳጆ ስለ አገር አንድነት፣ ነፃነትና እኩልነት ሲያዜም ኖሯል ብሏል፡፡

የድምፃዊውን ኅልፈት ተከትሎ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ባስተላለፉት የሐዘን መልዕክት፣ በሙዚቃ ሥራዎቹ ለኦሮሞ ሕዝብ ትግል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስታውሰው፣ በሞት ቢለይም ከትውልድ ትውልድ ተሻጋሪ ሥራዎቹ ሲታወስ ይኖራል ብለዋል፡፡

በአፋን ኦሮሞ በርካታ ሥራዎችን ለሕዝብ በማድረስ አድናቆትና ተወዳጅነትን ያተረፈው ድምፃዊ ዘሪሁን፣ ለስኬቱ ከተቀበላቸው ሽልማቶች መካከል የሀጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ያበረከተለት ሽልማት ይጠቀሳል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለሰው ልጅ መብት መከበር ስናወራ 75 ዓመት ሞላን!

በገነት ዓለሙ ዓለም ስለሰብዓዊ መብቶች ሲያወራ፣ ሲምል፣ ሲገዘት፣ ሲፈጠም፣ ቃል...

ካልተማከለ የካፒታል ገበያ ወደ ዘመናዊና የተደራጀ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ

በእሱፈቃድ ተረፈ በአገራችን የካፒታል ገበያ አዋጅ መውጣትን ተከትሎ የተማከለ የሰነደ...

ለማይቀረው ምክክርና ድርድር እንዘጋጅ

በያሲን ባህሩ  የዘመናዊት ኢትዮጵያ ፖለቲካ ውዝግብ በትንሹ የአንድ ምዕተ ዓመት...

ደንብ አስከባሪዎች ደንብ ያክብሩ!

በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ አስከባሪዎች፣ ሌሎች የፀጥታ አካላት፣ እንዲሁም...