Tuesday, September 26, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየቂርቆስ ክፍለ ከተማ ያስገነባቸውን የዳቦ ፋብሪካና ፓርክ ለአገልግሎት ክፍት አደረገ

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ያስገነባቸውን የዳቦ ፋብሪካና ፓርክ ለአገልግሎት ክፍት አደረገ

ቀን:

በአዲስ አበበ ከተማ አስተዳደር ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ አራት ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት የሆኑት የዳቦ ፋብሪካና የቂርቆስ ፓርክ የበርካታ ዜጎችን ችግር የሚቀርፉ መሆናቸው ተገለጸ፡፡

ፕሮጀክቶቹ የተገነቡት በደቡብ ግሎባል ባንክና አቶ አየለ አርፍጮ በተባሉ በጎ ፈቃደኛ ባለሀብት ሲሆን፣ ፕሮጀክቶቹም በ90 ቀናት ውስጥ ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸውን ሚያዝያ 10 ቀን 2015 ዓ.ም. ተገልጿል፡፡

በቀን ከ300 ሺሕ እስከ 400 ሺሕ ዳቦና ኬክ የማምረት አቅም አለው የተባለው በረከት የዳቦና የኬክ ማምረቻ ፋበሪካ ለ120 ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥራልም ተብሏል፡፡

በተመሳሳይ በክፍለ ከተማው ቄራ አደባባይ አካባቢ የተገነባው የቂርቆስ ፓርክ በነዋሪዎች፣ በባለሀብቶችና በተቋማት ተሳትፎ መሆኑን የክፍለ ከተማው ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

በሦስት ሺሕ ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው ፓርኩ፣ ለከተማዋ ውበት ከመስጠቱም ባለፈ ለ100 ሰዎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን አክለዋል፡፡ 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የቤት ባለንብረቶች የሚከፍሉትን ዓመታዊ የንብረት ታክስ የሚተምን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በአዋጁ መሥፈርት መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የንብረት ታክስ መጠን...

እንደ ንብረት ታክስ ያሉ ወጪን የሚያስከትሉ አዋጆች ከማኅበረሰብ ጋር ምክክርን ይሻሉ!

የመንግሥትን ገቢ በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የሚታመኑት የተጨማሪ እሴት...

ለዓለምም ለኢትዮጵያም ሰላም እንታገል

በበቀለ ሹሜ ያለፉት ሁለት የዓለም ጦርነቶች በአያሌው የኃያል ነን ባይ...